ዝምታው (Zemetaw) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 3.jpg


(3)

ዝምታው
(Zemetaw)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:59
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

ሚነጋ ፡ አይመስልም ፡ ሌሊቱ ፡ ረዝሞ
ጨለማውን ፡ አይቶ
ሌሊቱም ፡ ያልፋል ፡ ደግሞም ፡ ይነጋል
ብርሃን ፡ ተክቶ
አይዘኝ ፡ ሃሳብ ፡ ትካዜ
ይሆናል ፡ ሁሉ ፡ በጊዜ (፪x)

አትጠጉት ፡ በቃ ፡ ድንጋይ ፡ አድርጉበት ፡ ሸትቷል ፡ መቃብሩ
ጠብቀነው ፡ ነበር ፡ በጊዜ ፡ እንዲመጣ ፡ አክትሟል ፡ ነገሩ
ሰው ፡ ደክሞት ፡ ሲጨርስ ፡ ኢየሱስ ፡ እርሱ ፡ ይጀምራል
በሞተ ፡ ነገር ፡ ላይ ፡ ይፈርዳል ፡ ሕይወት ፡ ይሰጠዋል

ዝምታው ፡ ቢያስገርም ፡ የማያይ ፡ ቢመስልም
አይቸኩል ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ ይፈርዳል ፡ በጊዜው
ታማኝ ፡ ነው ፡ ታማኝ ፡ ነው

ሚነጋ ፡ አይመስልም ፡ ሌሊቱ ፡ ረዝሞ
ጨለማውን ፡ አይቶ
ሌሊቱም ፡ ያልፋል ፡ ደግሞም ፡ ይነጋል
ብርሃን ፡ ተክቶ
አይዘኝ ፡ ሃሳብ ፡ ትካዜ
ይሆናል ፡ ሁሉ ፡ በጊዜ (፪x)

ልቧ ፡ ያዘነባት ፡ ሁሌ ፡ ምታለቅሰው ፡ ልጅ ፡ የሌላት ፡ ሃና
ታሾፍባት ፡ ነበር ፡ ነገ ፡ የሚሆነው ፡ ያልገባት ፡ ፍናና
በጊዜው ፡ ፈረደ ፡ አምላኳ ፡ እንባዋን ፡ አበሰ
ትውልድ ፡ የሚያወሳው ፡ ልጅ ፡ ሰጣት ፡ ሕይወቷ ፡ ተካሰ

ዝምታው ፡ ቢያስገርም ፡ የማያይ ፡ ቢመስልም
አይቸኩል ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ ይፈርዳል ፡ በጊዜው
ታማኝ ፡ ነው ፡ ታማኝ ፡ ነው

አንዳንዶች ፡ እንደዚህ ፡ ናቸው
መከራው ፡ ሲበዛባቸው
እምነታቸውን ፡ ሲጥሉ
አይሰማም ፡ አያይም ፡ ሲሉ
አለ ፡ ሁሉንም ፡ የሚያይ
ከላይ ፡ ከሰማይ (፪x)

ስለዚህ ፡ አትታበዩ
በኩራት ፡ አትናገሩ
እግዚአብሔር ፡ ሁሉን ፡ ያውቃል
ይፈርዳል ፡ ይፈርዳል