ደሞ ፡ ተነሳ (Demo Tenesa) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

M

ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 3.jpg


(3)

ዝምታው
(Zemetaw)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:14
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

ይውለቅ ፡ ከላዬ ፡ ላይ ፡ ይህ ፡ የክብር ፡ ልብሴ
በፊቱ ፡ ላሸብሽብ ፡ ታመስግነው ፡ ነፍሴ
አይገደኝም ፡ እኔ ፡ ያሉኝን ፡ ቢሉኝ
ታቦቱ ፡ ከፊቴ ፡ ቤቴ ፡ ቀርቦልኝ

ክብር ፡ ይሁን ፡ ክብር ፡ ይሁን
ክብር ፡ ይሁን ፡ ክብር ፡ ይሁን

ደግሞ ፡ ተነሳ ፡ ልቤ ፡ እንደገና
ከየት ፡ እንዳነሳኝ ፡ ትዝ ፡ አለኝና ፡ ትዝ ፡ አለኝና
አልቻልኩበትም ፡ ዝም ፡ ማለት
ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ይሁንለት ፡ ይሁንለት
ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ይሁንለት ፡ ይሁንለት

ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ ባርኪው ፡ አምላክሽን ፡
ከወደቅሽበት ፡ ያነሳሽን ፡
ውለታውን ፡ እንዳትረሺ
ለምሥጋን ፡ ሁሌ ፡ ተነሺ

ማን ፡ ነበረ ፡ ያኔ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ
በበረሃው ፡ ላይ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ
እየደጋገፈ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ
ያም ፡ ዘመን ፡ አለፈ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ

አምልኮዬን ፡ ይዤ ፡ አደባባይ ፡ ልውጣ
ያኮራኛል ፡ እንጂ ፡ አላፍርም ፡ በጌታ

የረዳኝ ፡ ይክበር ፡ ጌታዬ '
ያገዘኝ ፡ ይክበር ፡ ጌታዬ

ደግሞ ፡ ተነሳ ፡ ልቤ ፡ እንደገና
ከየት ፡ እንዳነሳኝ ፡ ትዝ ፡ አለኝና ፡ ትዝ ፡ አለኝና
አልቻልኩበትም ፡ ዝም ፡ ማለት
ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ይሁንለት ፡ ይሁንለት
ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ይሁንለት ፡ ይሁንለት

ከአዳኝ ፡ ወጥመድ ፡ እያስመለጠ
እባቡን ፡ ጊንጡን ፡ እያስረገጠ
እኔ ፡ ያልዘመርኩኝ ፡ ማን ፡ ሊዘምር
ተደርጐልኝ ፡ ብዙ ፡ ተዓምር

ማን ፡ ነበረ ፡ ያኔ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ
በበረሃው ፡ ላይ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ
እየደጋገፈ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ
ያም ፡ ዘመን ፡ አለፈ ፡ እርሱ ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከጐኔ ፡ ሆኖ ፡ ያበረታኝ

አምልኮዬን ፡ ይዤ ፡ አደባባይ ፡ ልውጣ
ያኮራኛል ፡ እንጂ ፡ አላፍርም ፡ በጌታ

የረዳኝ ፡ ይክበር ፡ ጌታዬ '
ያገዘኝ ፡ ይክበር ፡ ጌታዬ

እዩአት ፡ ስትከፋ ፡ ሜልኮል
በአምላኬ ፡ ፊት ፡ ሳሸበሽብ
ውርደት ፡ መስሏት ፡ ክብሬን ፡ መጣሌ
በእርሱ ፡ አይደል ፡ ወይ ፡ በሕይወት ፡ መኖሬ
ሰማይን ፡ ለሰራ ፡ ምድርን ፡ ለዘረጋ
ላለና ፡ ለሚኖር ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ

ከዚህ ፡ በላይ ፡ እሆናለሁ
ገና ፡ ገና ፡ እሆናለሁ
አባቴ ፡ ነው ፡ እሆናለሁ
እወደዋለሁ ፡ እሆናለሁ

እዩአት ፡ ስትከፋ ፡ ሜልኮል
በአምላኬ ፡ ፊት ፡ ሳሸበሽብ
ውርደት ፡ መስሏት ፡ ክብሬን ፡ መጣሌ
በእርሱ ፡ አይደል ፡ ወይ ፡ በሕይወት ፡ መኖሬ
ሰማይን ፡ ለሰራ ፡ ምድርን ፡ ለዘረጋ
ላለና ፡ ለሚኖር ፡ አልፋና ፡ ኦሜጋ

ከዚህ ፡ በላይ ፡ እሆናለሁ
ገና ፡ ገና ፡ እሆናለሁ
አባቴ ፡ ነው ፡ እሆናለሁ
እወደዋለሁ ፡ እሆናለሁ
ሕይወቴ ነው ፡ እሆናለው
ኣ...


END