ቢበራማ (Biberama) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 3.jpg


(3)

ዝምታው
(Zemetaw)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 5:55
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

በመንገዴ ፡ ስሄድ ፡ ስራመድ ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና
እግሮቼ ፡ በቤትህ ፡ ጸንተው ፡ ዓይኔ ፡ ግን ፡ ሳይበራ
የሚሄደው ፡ የሚመጣው ፡ ሲያዳክመው ፡ ፡ ልቤን
የቆምኩኝ ፡ ያለሁኝ ፡ መስሎኝ ፡ እያንገዳገደኝ
አልገባኝም ፡ ነበር ፡ የልቦና ፡ ዓይኔ ፡ ታውሮ
ምድር ፡ ምድር ፡ አለ ፡ የከበረውን ፡ ሰማይን ፡ ጥሎ

ቃልህን ፡ ስሰማ ፡ ልቤ ፡ ተደስቶ
ለጊዜው ፡ ነበረ ፡ በስሜት ፡ ተገፍቶ
ነፋስና ፡ ጐርፉ ፡ ሊፈትነኝ ፡ መጣ
ይታወቀኝ ፡ ጀመር ፡ ከመንገድ ፡ ስወጣ

ቢበራማ ፡ በቃልህ ፡ ቢጸና ፡ ዓይኔ ፡ ቢበራ
ቢበራማ ፡ ጸንቶ ፡ ይቆም ፡ ነበር ፡ ፍሬ ፡ እያፈራ
ቢበራማ ፡ ቅርንጫፍ ፡ ከግንዱ ፡ ከተጣበቀ
ቢበራማ ፡ ያስታውቃል ፡ መልኩ ፡ አንተን ፡ ያወቀ

ዓይኖቼን ፡ አብራ ፡ ክፈት ፡ ዓይኔን
እነደ ፡ እኔ ፡ ሳይሆን ፡ እንዳንተ ፡ እንዳይ

በመንገዴ ፡ ስሄድ ፡ ስራመድ ፡ በሕይወት ፡ ጐዳና
እግሮቼ ፡ በቤትህ ፡ ጸንተው ፡ ዓይኔ ፡ ግን ፡ ሳይበራ
የሚሄደው ፡ የሚመጣው ፡ ሲያዳክመው ፡ ፡ ልቤን
የቆምኩኝ ፡ ያለሁኝ ፡ መስሎኝ ፡ እያንገዳገደኝ
አልገባኝም ፡ ነበር ፡ የልቦና ፡ ዓይኔ ፡ ታውሮ
ምድር ፡ ምድር ፡ አለ ፡ የከበረውን ፡ ሰማይን ፡ ጥሎ

ሲዘነጋ ፡ ለቤ ፡ የሰማዩን ፡ ቤቱን
በዚህ ፡ ምድር ፡ሲኖር ፡ እንግዳ ፡ መሆኑን
አይጐመጅም ፡ ነበር ፡ ለምድራዊው ፡ ኑሮ
የሰማዩን ፡ ዓለም ፡ አንዴ ፡ ቢያየው ፡ ኖሮ

ቢበራማ ፡ የተጠራበትን ፡ የክብር ፡ ተስፋ
ቢበራማ ፡ የዘላለም ፡ እርስት ፡ ከቶ ፡ ማይጠፋ
ቢበራማ ፡ ዓይኖቼ ፡ ተከፍቶ ፡ ይህንን ፡ ቢያይ
ቢበራማ ፡ ይናፍቃል ፡ ልቤ ፡ ወደ ፡ ሰማይ

ዓይኖቼን ፡ አብራ ፡ ክፈት ፡ ዓይኔን
እነደ ፡ እኔ ፡ ሳይሆን ፡ እንዳንተ ፡ እንዳይ

ልመናዬ ፡ ይሄ ፡ ነው
አብራው ፡ ዓይኔን