ደስ ፡ የሚልህን ፡ ስጦታ (Des Yemilehen Setota) - ዮሐንስ ፡ ግርማ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ ግርማ
(Yohannes Girma)

Yohannes Girma 2.jpg


(2)

እርስቴ ፡ ነህ
(Erestie Neh)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 4:39
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ ግርማ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Girma)

ደስ ፡ የሚልህን ፡ ስጦታ
በእጄ ፡ ያለኝን ፡ ጌታ
ራሴን ፡ ላድርግ ፡ መስዕዋትህ
ከሁሉ ፡ በላይ ፡ የምሰጥህ
ኑሮህን ፡ ጨርሰህ ፡ በእኔ ፡ ኑር
ካሰብከው ፡ የሚቀርህ ፡ አይኑር (፪x)

በአንተ ፡ መኖር ፡ ያሰብከውን ፡ መኖር
ኑሮህን ፡ መኖር ፡ መርጫለሁ
ብኖር ፡ ለአንተ
ብሞትም ፡ ለአንተ
ከፈቃድህ ፡ ስር ፡ ይሁን ፡ መቃብሬ
ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ኑሮ/ሕይወት ፡ አይታየኝም ፡ እኔ (፪x)

በላይ ፡ ያለው ፡ ፈቅድህ
በምድር ፡ በእኔ ፡ እንዲሆን
ይኸው ፡ ራሴን ፡ አምጥቻለሁ
ለአንተ ፡ እንዲሆን ፡ ሰጥቻለሁ
ለክብርህ ፡ መገለጫ ፡ ዕቃ
የወደድከውን ፡ ማድረጊያ (፪x)

እንደ ፡ ወትሮው ፡ በሥጋዬ
ከብሮ ፡ ሳየው ፡ ውድ ፡ ጌታዬ
ልጁን ፡ በእኔ ፡ መልክ ፡ ገልጦት
ያሰበውም ፡ ሰምሮለት
ደስታዬ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ ይሞላል
መሻቴ ፡ ፍጻሜን ፡ ያገኛል (፪x)

በአንተ ፡ መኖር ፡ ያሰብከው ፡ መኖር
ኑሮህን ፡ መኖር ፡ መርጫለሁ
ብኖር ፡ ለአንተ
ብሞትም ፡ ለአንተ
ከፈቃድህ ፡ ስር ፡ ይሁን ፡ መቃብሬ
ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ኑሮ/ሕይወት ፡ አይታየኝም ፡ እኔ (፪x)