ግን ፡ ባንተ (Gin bante) (3) - ይድነቃቸው ተካ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ይድነቃቸው ተካ
(Yidnekachew Teka)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(2)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ ፩ (2016)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:31
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የይድነቃቸው ተካ ፡ አልበሞች
(Albums by Yidnekachew Teka)

ደካማ ሆኜ አገኘኸኝ
ኃጥያተኛ ሆኜ አገኘኸኝ
የማልጠቅም ሆኜ አገኘኸኝ
ከሰይጣን እጅ ሆኜ አገኘኸኝ
ግን ባንተ ከዚህ ሁሉ ወጥቻለሁ
ግን ባንተ የእግዚአብሔር ልጅ ተብያለሁ
ግን ባንተ ከዚህ ሁሉ ወጥቻለሁ
ግን ባንተ የእግዚአብሔር ልጅ ተብያለሁ
ዛሬ አርገኸኛል የብርሃን ልጅ እኔን
ኢየሱስ ወሰደህ ጨለማዬን /4* /
 
ይቺ ፅዋ ከኔ ትለፍ ብትል እንኳ
ኢየሱስ ታዘአል እንዳያልፈኝ የሕይወት ፅዋ የእግዚአብሔር በግ
አስቀድመህ የታረድከው
ሌባው እንዳያርደኝ እንዳልጠፋ እንዳልሞት ነው
ለምን ተውከኝ ብለህ ስትጮህ አብ ዝም ያለህ
እኔ እንዳልጣል እንዳልተው ሁሌ ፊትህ
ደዌ እመሜን ተቀበልህ ተሸከምህ
እኔ ያንተን ሕይወት ደኅንነትን እንድቀበል
የብርሃን መልዕክቴ ነህ ኢየሱስ ልቤ ላይ በራህ
ሰማሁህ የምስራቼ ድኛለሁ ወንጌል ሰምቼ
በአመድ ፈንታ ሆነኽልኛል አክሊሌ
በለቅሶ ፈንታ የደስታ ዘይት ነሆ ለኔ
በአዘን ፈንታ የደስታ መጎናፀፊያ
አረከኝ እኔን የምሕረትህ ማሳያ
 
ጋሻ ሆነህ ግን ተወጋህ ጎንህን
እረኛ የሆንከው ልክ እንደ በግ ተነዳህ
የአለም ጌታ በምድር ጌታ ፊት ቆመሀል
ምንጭ የሆንከው አንተ የኔ ኢየሱስ ተጠምተአል
እንደ ፀሐይ የሚያበራ ፊት እያለህ
ግን እኔ እንዳበራ እንድደምቅ ተተፋብህ
ሰማይ ምድርን የምትጠቀልል ልክ እንደ ጨርቅ
ግን ኢየሱስ ለኔ ተጠቅልለህ መቃብር ሆንክ
ይሁን ስትል የሚሆንልህ
አንተ ላይ ይሁን አሉብህ
ግን ዝም አልክ አልመለስክም
አይተህ ነው እኔን ደስታህን
ለወጉህ እጆች ኃይላቸው ነበርክ ፈጣሪ
ለሰደቡህ አፎች አንተ ነህ የእነርሱ ሰሪ
ፈቀድክላቸው አልከለከልካቸውም
የምትሞተው በጦር ለወጉህ ለእነርሱም