ያ ፡ ሁሉ ፡ አለፈና (Ya Hulu Alefena) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Lyrics.jpg


(1)

ባማረ ፡ ቅኔ
(Bamare Qenie)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 6:04
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)


አዝ፦ እንደማያልፍ ፡ የለም ፡ ያሁሉ ፡ አለፈና
የሰቆቃው ፡ ዘመን ፡ በደስታ ፡ ተተካ ፡ አሜን
አንገቴን ፡ ደፍቼ ፡ የሰው ፡ ፊት ፡ ፈርቼ
ያለፍኩበት ፡ ዘመን ፡ ዘለፋ ፡ ጠግቤ ፡ አቤት
በቃ ፡ ሲለኝ ፡ ጌታ ፡ ወደ ፡ ገደል ፡ ገባ
የጐበጠ ፡ አንገቴ ፡ ለምሥጋና ፡ ቀና ፡ አሜን (፪x)

ምሥጋናዬ ፡ ይህ ፡ ነው ፡ ምሥጋናዬ
አሰዋለሁ ፡ ዛሬ ፡ በኮረብታ ፡ ቆሜ
ነጻ ፡ ወጥቼ ፡ ነጻ ፡ ሰው ፡ መሆን ፡ ችያለሁ
በክርስቶስ ፡ ዛሬ ፡ ትልቅ ፡ ተብያለሁ
የናቁኝም ፡ ያኔ ፡ አንቅረው ፡ የተፉኝ
ጐንበስ ፡ አሉ ፡ ጐንበስ ፡ ጌታ ፡ አክብሮኝ ፡ ሲያዩኝ

አዝ፦ እንደማያልፍ ፡ የለም ፡ ያሁሉ ፡ አለፈና
የሰቆቃው ፡ ዘመን ፡ በደስታ ፡ ተተካ ፡ አሜን
አንገቴን ፡ ደፍቼ ፡ የሰው ፡ ፊት ፡ ፈርቼ
ያለፍኩበት ፡ ዘመን ፡ ዘለፋ ፡ ጠግቤ ፡ አቤት
በቃ ፡ ሲለኝ ፡ ጌታ ፡ ወደ ፡ ገደል ፡ ገባ
የጐበጠ ፡ አንገቴ ፡ ለምሥጋና ፡ ቀና ፡ አሜን

አሁን ፡ ይኸው ፡ እንዲህ ፡ እንዲህ ፡ አምሮብኛል
አፌም ፡ በዝማሬ ፡ በዘይት ፡ ታብሷል
ማንም ፡ አልጠበቀኝ ፡ እኔን ፡ ለቁም ፡ ነገር
ጌታ ፡ ሲያረገው ፡ ግን ፡ ማነው ፡ የሚናገር
ምስኪኖች ፡ ሆይ ፡ በርቱ ፡ ጌታ ፡ አይጥላችሁም/ሰውን ፡ አይጥልም
ምስክር ፡ ነኝ ፡ እኔ ፡ በዓይኔ ፡ ስላየሁኝ (፪x)

አዝ፦ እንደማያልፍ ፡ የለም ፡ ያሁሉ ፡ አለፈና
የሰቆቃው ፡ ዘመን ፡ በደስታ ፡ ተተካ ፡ አሜን
አንገቴን ፡ ደፍቼ ፡ የሰው ፡ ፊት ፡ ፈርቼ
ያለፍኩበት ፡ ዘመን ፡ ዘለፋ ፡ ጠግቤ ፡ አቤት
በቃ ፡ ሲለኝ ፡ ጌታ ፡ ወደ ፡ ገደል ፡ ገባ
የጐበጠ ፡ አንገቴ ፡ ለምሥጋና ፡ ቀና ፡ አሜን

ያኔ ፡ ያሰብኩት ፡ ሁሉ ፡ ወደ ፡ ገደል ፡ ገብቷል
አሁን ፡ በሕይወቴ ፡ ዛሬ ፡ አካሌ ፡ ቆሟል
ወገኖችም ፡ በቃ ፡ ብለው ፡ ነበር ፡ በቃ
በሃያሉ ፡ ኢየሱስ ፡ ከመቃብር ፡ ወጣሁ
እግሬም ፡ እንደዋላ ፡ አግሮች ፡ በርትተዋል
አፌም ፡ በዝማሬ ፡ በዘይት ፡ ታብሷል

አዝ፦ እንደማያልፍ ፡ የለም ፡ ያሁሉ ፡ አለፈና
የሰቆቃው ፡ ዘመን ፡ በደስታ ፡ ተተካ ፡ አሜን
አንገቴን ፡ ደፍቼ ፡ የሰው ፡ ፊት ፡ ፈርቼ
ያለፍኩበት ፡ ዘመን ፡ ዘለፋ ፡ ጠግቤ ፡ አቤት
በቃ ፡ ሲለኝ ፡ ጌታ ፡ ወደ ፡ ገደል ፡ ገባ
የጐበጠ ፡ አንገቴ ፡ ለምሥጋና ፡ ቀና ፡ አሜን (፪x)