ንገስልኝ (Negeselegn) - ተከስተ ፡ ጌትነት

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተከስተ ፡ ጌትነት
(Tekeste Getnet)

Tekeste Getnet Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

ነገሥታት ፡ ቢቀየሩ
(Negestat Biqeyeru)

ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተከስተ ፡ ጌትነት ፡ አልበሞች
(Albums by Tekeste Getnet)

እግዚአብሔርን ፡ በመተማመን ፡ ተግተው ፡ የሚጠባባቁ (፪x)
ከመልካም ፡ ነገር ፡ አይጎድሉም ፡ በመከራ ፡ ቀን ፡ አይወድቁ (፪x)
ለደካሞችም ፡ ኃይላቸው ፡ ነውና ፡ እንደሚለው ፡ ቃሉ (፪x)
የረዳችሁ ፡ ያገዛችሁ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ክበር ፡ በሉ (፪x)

አዝክበርልኝ (፪x)
በአንተ ፡ ነውና ፡ ያማረብኝ
ንገስልኝ (፪x)
በአንተ ፡ ነውና ፡ ሰው ፡ የሆንኩኝ
ክበር ፡ ክበርልኝ (፪x)
ንገስ ፡ ንገስልኝ (፪x)

ቆይቼ ፡ ደጅ ፡ ጠናሁት ፡ እሱም ፡ ዘንበል ፡ አለልኛ (፪x)
ታምኜው ፡ አላሳፈረኝ ፡ ጌታ ፡ እውነተኛ ፡ ዳኛ (፪x)
ጠብቆ ፡ ያልከሰረ ፡ የወጣ ፡ ከጭንቅ ፡ ከማጡ (፪x)
ያክብረው ፡ በዝማሬ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ክብርን ፡ ያምጡ (፪x)

አዝክበርልኝ (፪x)
በአንተ ፡ ነውና ፡ ያማረብኝ
ንገስልኝ (፪x)
በአንተ ፡ ነውና ፡ ሰው ፡ የሆንኩኝ
ክበር ፡ ክበርልኝ (፪x)
ንገስ ፡ ንገስልኝ
ንገስ ፡ ንገስልኝ (፪x)