ከማመልክህ (Kemamlekeh) - ሮማን ፡ ሎሬንሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሮማን ፡ ሎሬንሶ
(Roman Lorenso)

Lyrics.jpg


(1)

ጌታ ፡ ብቻ ፡ ታማኝ ፡ ነው
(Gieta Becha Tamagn New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሮማን ፡ ሎሬንሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Roman Lorenso)

አዝ፦ ከማመልክህ ፡ ከአንተ ፡ በቀር
ሌላ ፡ አምላክ ፡ አላውቅም ፡ (አላውቅም) (፪x)
አምላኬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ንጉሤ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ተስፋዬም ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም

አንተ ፡ አምላኬ ፡ ነህ ፡ መድኃኒቴ
የምታመንብህ ፡ ረዳቴ
ወደ ፡ ቀኝም ፡ ወደ ፡ ግራም ፡ አልልም
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ሌላ ፡ አምላክ ፡ አላውቅም
(፪x)

አዝ፦ ከማመልክህ ፡ ከአንተ ፡ በቀር
ሌላ ፡ አምላክ ፡ አላውቅም ፡ (አላውቅም) (፪x)
አምላኬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ንጉሤ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ተስፋዬም ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም

በክንፎችህ ፡ ጥላ ፡ ደስ ፡ ይለኛልና
አምባ ፡ መጠጊያዬም ፡ ሆነኸኛልና
በአንተ ፡ ሆኜ ፡ እፍረት ፡ አግኝቻለሁ
አምላኬ ፡ ሆይ ፡ እባርክሃለሁ
(፪x)

አዝ፦ ከማመልክህ ፡ ከአንተ ፡ በቀር
ሌላ ፡ አምላክ ፡ አላውቅም ፡ (አላውቅም) (፪x)
አምላኬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ንጉሤ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ጋሻዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም

ሳልናወጥ ፡ እኔ ፡ መቀመጤ
ኤልሻዳይ ፡ በሆንከው ፡ በአንተ ፡ ነው ፡ ጌታዬ
ለእኔ ፡ አንተ ፡ ንህ ፡ ከማንም ፡ ይልቅ
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ትምክህት ፡ ከእኔ ፡ ይራቅ
(፪x)

አዝ፦ ከማመልክህ ፡ ከአንተ ፡ በቀር
ሌላ ፡ አምላክ ፡ አላውቅም ፡ (አላውቅም) (፪x)
አምላኬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ንጉሤ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ተስፋዬም ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም

በምህረትህ ፡ እንደ ፡ ንስር ፡ ተሸከምከኝ
ስንቱን ፡ ውጣ ፡ ውረድ ፡ ጌታ ፡ አሳለፍከኝ
ባገኘኝም ፡ በታላቅ ፡ መከራ
ኃይል ፡ ሆንክልኝ ፡ አምላኬ ፡ እንዳልፈራ
(፪x)

አዝ፦ ከማመልክህ ፡ ከአንተ ፡ በቀር
ሌላ ፡ አምላክ ፡ አላውቅም ፡ (አላውቅም) (፪x)
አምላኬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ንጉሤ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም ፡ (ዘለዓለም)
ተስፋዬም ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ዘለዓለም