ቅዱስ ፡ ቅዱስ (Qedus Qedus) - ረዳ ፡ አብርሃም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ረዳ ፡ አብርሃም
(Redda Abraham)

Lyrics.jpg


(1)

አልጥልህም ፡ አልተውህም
(Altelehem Altewehem)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 6:03
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የረዳ ፡ አብርሃም ፡ አልበሞች
(Albums by Redda Abraham)

አዝቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ለሰራዊት ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር (፪x)

በነጩ ፡ ዙፋን ፡ ተቀምጠሃል
አክሊላቸውን ፡ ያወሩልሃል
ሁሉን ፡ ፈጥረሃል ፡ ፈቃድህ ፡ ሆኗል
እጅግ ፡ ትልቅ ፡ ነህ ፡ ማን ፡ ይመስልሃል

አዝቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ለሰራዊት ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር (፪x)

መልክህ ፡ እንዲህ ፡ ነው ፡ አንተ ፡ ትልቁ
. (1) .
ቀስተደመና ፡ ማዕረግህ ፡ ዙሪያህ
ከቦ ፡ ይልሃል ፡ ኃያል ፡ ቅዱስ ፡ ነህ

አዝቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ለሰራዊት ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር (፪x)

እልፍ ፡ ጊዜ ፡ እልፍ ፡ ሺህም ፡ ጊዜ ፡ ሺህ
የምትመለክ ፡ በመላእክትህ
በኪሩቤል ፡ ላይ ፡ ምትመላለስ
እግዚአብሔር ፡ አምላክ ፡ ዘላለም ፡ ቅዱስ

አዝቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
የሰራዊት ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር (፪x)

ነገሥታት ፡ ሲያልፉ ፡ ሲለዋወጡ
አንተ ፡ ግን ፡ ሕያው ፡ ሁልጊዜ ፡ ብርቱ
በቅንድቦችህ ፡ ሰውን ፡ መርማሪ
መሳይ ፡ የሌለህ ፡ ተወዳዳሪ

አዝቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
የሰራዊት ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር (፪x)

ከእስራት ፡ ፈቺ ፡ ቀንበር ፡ ሰባሪ
በጽድቅ ፡ ዙፋን ፡ ዘላለም ፡ ኗሪ
ማደሪያህ ፡ ቅዱስ ፡ አንተ ፡ ቅዱስ ፡ ነህ
ሰማይ ፡ ምድር ፡ ሲያልፍ ፡ በክብር ፡ አለህ

አዝቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
ቅዱስ (፬x) ፡ ኃያል (፬x)
የሰራዊት ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር (፮x)