የኢየሱስ ፡ ሥም (Yeyesus Sem) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 7.jpg


(7)

የታመንኩትን ፡ አውቃለሁ
(Yetamenkuten Awqalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 4:50
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

ከጠላቴ ፡ ጋራ ፡ ስሟገት
ነፍሴም ፡ አታ ፡ ሳለ ፡ እረፍት
ወደ ፡ ተራሮችም ፡ አየሁ
እረዳት ፡ ግን ፡ ምንም ፡ አጣሁ
ግን ፡ መድሃኒቴን ፡ ስጠራው
ሲበራ ፡ አየሁ ፡ የድል ፡ ጮራው

አዝ፦ የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ኃይል ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ጉልበት ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ፈውስ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ከሥሞች ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

አልናድ ፡ ያለው ፡ ተራራ
ተናደ ፡ የሱን ፡ ሰም ፡ ስጠራ
አልሞላ ፡ ያለ ፡ ሸለቆ
ታየኝ ፡ በጌታዬ ፡ ሞልቶ
በታምራቱ ፡ አስደነቀኝ
የስሙን ፡ ኃይል ፡ አሳየኝ

አዝ፦ የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ኃይል ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ጉልበት ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ፈውስ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ከሥሞች ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

ሞቴን ፡ በሞቱ ፡ የሻረው
ስሞ ፡ መድሃኒቴ ፡ የሆነው
እስከ ፡ ዛሬም ፡ አልተረታ
ዘላለም ፡ የማይረታ
ለእርሱ ፡ ልዘምር ፡ በደስታ
ይክበር ፡ እያልኩ ፡ በዕልልታ

አዝ፦ የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ኃይል ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ጉልበት ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ፈውስ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ከሥሞች ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

እያሪኮ ፡ ቢሆን ፡ ጐልያድ
በፊታችሁ ፡ ቢገደገድ
የኢየሱስን ፡ ሥም ፡ ስንጠራ
ይወድቃሉ ፡ በየተራ
ከሥሞች ፡ በላይ ፡ ሥም ፡ ያለው
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ታላቅ ፡ ነው

አዝ፦ የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ኃይል ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ጉልበት ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ፈውስ ፡ ነው
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ከሥሞች ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)