እዘምራለሁ (Ezemralehu) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
Broom.png ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Lyrics.jpg


()

ምሥጋና ፡ መልካም ፡ ነው
(Mesgana Melkam New)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:29
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝ፦ ምህረቱን ፡ ቸርነቱን
እዘምራለሁ ፡ እንዴት ፡ ዝም ፡ ልል ፡ እችላለሁ
እዘምራለሁ ፡ እጅግ ፡ ፈሶልኝ ፡ አይቻለሁ (፪x)

አብዝቼ ፡ ልወደው ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል
ብዙ ፡ የነበረው ፡ ኃጢአቴ ፡ ተፍቋል
ዝቅ ፡ ብዬ ፡ እግሮቹን ፡ በእምባዬ ፡ ላርሰው
ብልቃቱም ፡ ይሰበር ፡ ሽቶውን ፡ ላፍስሰው (፪x)

አዝ፦ ምህረቱን ፡ ቸርነቱን
እዘምራለሁ ፡ እንዴት ፡ ዝም ፡ ልል ፡ እችላለሁ
እዘምራለሁ ፡ እጅግ ፡ ፈሶልኝ ፡ አይቻለሁ

የኃጢአተኛ ፡ ወዳጅ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ተባለ
ዘኪዮስ ፡ ሆይ ፡ ቤትህ ፡ ውላለው ፡ ስላለ
ዛሬ ፡ ቀን ፡ ለዚህ ፡ ቤት ፡ መዳን ፡ ሆኖለታል
ብሎ ፡ መድኃኒቴ ፡ ምህረትን ፡ አውጇል (፪x)

አዝ፦ ምህረቱን ፡ ቸርነቱን
እዘምራለሁ ፡ እንዴት ፡ ዝም ፡ ልል ፡ እችላለሁ
እዘምራለሁ ፡ እጅግ ፡ ፈሶልኝ ፡ አይቻለሁ

ምህረቱ ፡ ያዘኝ ፡ ከቤቱ ፡ እንዳልወጣ
ቸርነቱ ፡ በዛ ፡ አንዳች ፡ እንዳላጣ
በሕይወቴ ፡ ዘመን ፡ እያተከተሉኝ
አምላኬ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ በቤትህ ፡ አኖሩኝ (፪x)

አዝ፦ ምህረቱን ፡ ቸርነቱን
እዘምራለሁ ፡ እንዴት ፡ ዝም ፡ ልል ፡ እችላለሁ
እዘምራለሁ ፡ እጅግ ፡ ፈሶልኝ ፡ አይቻለሁ