እነሆ ፡ የዓለምን ፡ ኃጢአት ፡ የሚያስወግድ (Eneho Yealemen Hatiyat Yemiyasweged) - መሠረት ፡ ፅጌና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 2.jpg


(2)

ዝናህ ፡ የገነነው
(Zenah Yegenenew)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

ለሰው ፡ ሁሉ ፡ የሚያበራው
እውነተኛው ፡ የዓለም ፡ ብርሃን
በዓለም ፡ ውስጥ ፡ የነበረው
ዓለሙ ፡ ግን ፡ ያላወቀው

አዝ፦ እነሆ ፡ የዓለምን ፡ ኃጢአት ፡ የሚያስወግድ
ዮሐንስ ፡ የመሰከረለት ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ (፪x)

ለተቀበሉት ፡ ሁሉ ፡ ግን ፡ በስሙም ፡ ለሚያምኑም
የእግዚአብሔር ፡ ልጆች ፡ ይሆኑ ፡ ዘንድ
ስልጣንንም ፡ ሰጣቸው

አዝ፦ እነሆ ፡ የዓለምን ፡ ኃጢአት ፡ የሚያስወግድ
ዮሐንስ ፡ የመሰከረለት ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ (፪x)

እውነትን ፡ ተሞልቶ ፡ በእኛ ፡ ውስጥ ፡ ያደረ
ኢየሱስ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ቀኝ ፡ የከበረ
እግዚአብሔርን ፡ የለም ፡ ያየው
በአባቱ ፡ እቅፍ ፡ ያለው ፡ ግን ፡ ተረከው

አዝ፦ እነሆ ፡ የዓለምን ፡ ኃጢአት ፡ የሚያስወግድ
ዮሐንስ ፡ የመሰከረለት ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ (፪x)