እግዚአብሔር ፡ ቤትን (Egziabhier Bieten) - መቅረዝ ፡ የወጣቶች ፡ አገልግሎት

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መቅረዝ ፡ የወጣቶች ፡ አገልግሎት
(Mekrez Youth Ministry)

Mekrez Youth Ministry 4.jpeg


(4)

አየዋለሁ ፡ መስቀሉን
(Ayewalehu Mesqelun)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2009)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመቅረዝ ፡ የወጣቶች ፡ አገልግሎት ፡ አልበሞች
(Albums by Mekrez Youth Ministry)

እግዚአብሔር ፡ ቤትን ፡ ካልሰራ ፡ ሰራተኞች ፡ በከንቱ ፡ ይደክማሉ
እግዚአብሔር ፡ ከተማን ፡ ካልጠበቀ ፡ ጠባቂዎች ፡ በከንቱ ፡ ይደክማሉ
ሃብትና ፡ በረከት ፡ ከአባት ፡ ይወረሳል
መልካምን ፡ ሴትን ፡ ግን ፡ ማንስ ፡ ያገኛታል
ሃሃሃሃሃ ፡ ሃሃሃሃሃ

እግዚአብሔር ፡ በረከትን ፡ ካልሰጠ
ሰዎች ፡ ሁሉ ፡ በከንቱ ፡ ይሮጣሉ
የግዚአብሄር ፡ በረከቱ ፡ ታላቅ ፡ ናት
በእርሷም ፡ ዘንድ ፡ ሃዘንም ፡ የለባት
ዋጋዋ ፡ ከቀይ ፡ ዕንቁ ፡ እጅግ ፡ የላቀ ፡ ነው
ለባሏም ፡ ዘውድ ፡ ናት ፡ ማንስ ፡ ያገኛታል
ሃሃሃሃሃ ፡ ሃሃሃሃሃ

እርሱ ፡ ግን ፡ በመንገዱ ፡ የሚሄድ
ፈቃዱንም ፡ የሚያደርግ
አምላኩን ፡ በፍፁም ፡ ልቡ ፡ የሚወድ
ለእርሱ ፡ ብቻ ፡ የሚሰጥ
እርሱ ፡ ያገኛታል ፡ ትዳሩም ፡ ይባረካል
በቤትም ፡ በከተማው ፡ ይሰምርለታል
ሃሃሃሃሃ ፡ ሃሃሃሃሃ