Endalkachew Hawaz/Mesganawen Alresawem/Mesganawen Alresawem
ምሥጋናውን ፡ አልረሳውም
- አዝ፦ ምሥጋናውን ፡ አልረሳውም
- ምህረቱን ፡ አልዘነጋውም
- ደስ ፡ ይለኛል ፡ በማዳኑ
- አመልከዋለሁኝ ፡ በየቀኑ (፪x)
- ያደረገልኝን ፡ ቆጥሬ
- አልጨርሰውም ፡ ተናግሬ
- ብዙ ፡ ነውና ፡ ምህረቱ
- ሥሙን ፡ አከብራለሁ ፡ በየዕለቱ (፪x)
- ምህረቱ ፡ እየበዛ ፡ ቁጣው ፡ ደግሞ ፡ እየዘገየ
- ከሰው ፡ ልጆች ፡ሁሉ: ይልቅ: በምክሩ ፡ የተለየ
- እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም (፬x)
- አዝ
- ምሥጋናውን አልረሳውም
- ምህረቱን አልዘነጋውም
- ደስ ይለኛል በማዳኑ
- አመልከዋለሁኝ በየቀኑ (፪x)
- ያደረገልኝን ቆጥሬ
- አልጨርሰውም ተናግሬ
- ብዙ ነውና ምህረቱ
- ሥሙን አከብራለሁ በየዕለቱ (፪x)
- ህጉ ለእግሬ ብርሃን ሆኖ
- ኢኸው ነፍሴን ፡ መልሷታል
- በጽድቅ መንገድ እየመራ
- በረከቱን አጥግቧታል
- ክበር ብለው ያንስበታል
- ንገሥ ብለው ያንስበታል (፪x)
አዝ
- ምሥጋናውን አልረሳውም
- ምህረቱን አልዘነጋውም
- ደስ ይለኛል በማዳኑ
- አመልከዋለሁኝ በየቀኑ (፪x)
- ያደረገልኝን ቆጥሬ
- አልጨርሰውም ተናግሬ
- ብዙ ነውና ምህረቱ
- ሥሙን አከብራለሁ በየዕለቱ
- ያደረገልኝን ቆጥሬ
- አልጨርሰውም ተናግሬ
- ብዙ ነውና ምህረቱ
- ሥሙን አከብራለሁ በየዕለቱ
- በመጥራቱ ሳይጸጸት
- ወደመንግሥቱ አፍልሶኛል
- አይጥለኝም አይተወኝም
- በእጆቹ መዳፍ ላይ ቀርጾኛል
- ክብሬን ጥዬ ባመሰግነው
- አይበዛበት ይህም ሲያንሰው ነው (፪x)
አዝ
- ምሥጋናውን አልረሳውም
- ምህረቱን አልዘነጋውም
- ደስ ይለኛል በማዳኑ
- አመልከዋለሁኝ በየቀኑ (፪x)
- ያደረገልኝን ቆጥሬ
- አልጨርሰውም ተናግሬ
- ብዙ ነውና ምህረቱ
- ሥሙን አከብራለሁ በየዕለቱ
- ያደረገልኝን ቆጥሬ
- አልጨርሰውም ተናግሬ
- ብዙ ነውና ምህረቱ
- ሥሙን አከብራለሁ በየዕለቱ