አንተ ፡ ገናና (Ante Genana) - ኤዶም ፡ ልዑልሰገድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤዶም ፡ ልዑልሰገድ
(Edom Leulseged)

Edom Leulseged 1.jpg


(1)

አንተ ፡ ገናና
(Ante Genana)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤዶም ፡ ልዑልሰገድ ፡ አልበሞች
(Albums by Edom Leulseged)

አዝ፦ አንተ ፡ ገናና ፡ ሆይ ፡ ሁሉን ፡ ትገዛለህ
አንተ ፡ ገናና ፡ ሆይ ፡ ሁሉን ፡ ትችላለህ
ችሎታህ ፡ ሳይለወጥ (፫x)
አቅምህም ፡ ሳይለወጥ (፫x)
ሁሉንም ፡ ታስተዳድራለህ
በፀጋህ ፡ ታስተዳድራለህ (፪x)
አመሰግንሃለሁ ፡ አመሰግንሃለሁ
አመሰግንሃለሁ ፡ አመሰግንሃለሁ (፪x)

ከፊቴ ፡ ስትቀድምልኝ ፡ እጄን ፡ ይዘህ ፡ ስታወጣኝ
ያለፈውን ፡ ክፉ ፡ ዘመን ፡ አሳልፈህ ፡ ስታስቀኝ
ታዲያ ፡ እንደዚህ ፡ አድርገህላኝ
እንዴት ፡ ችዬ ፡ ዝም ፡ እላለሁ
ተነስቼ ፡ ለአንተ ፡ ጌታ ፡ ምሥጋናዬን ፡ አቀርባለሁ

እንዴት ፡ ዝም ፡ እላለሁ ፡ እንደዚህ ፡ አድርገህልኝ
እንዴት ፡ ዝም ፡ እላለሁ ፡ ፀሎቴን ፡ ሰምተህልኝ
እንዴት ፡ ዝም ፡ እላለሁ ፡ ጠላቴን ፡ አባረህልኝ
እንዴት ፡ ዝም ፡ እላለሁ ፡ ሸለቆዬን ፡ ሞልተህልኝ

አዝ፦ አንተ ፡ ገናና ፡ ሆይ ፡ ሁሉን ፡ ትገዛለህ
አንተ ፡ ገናና ፡ ሆይ ፡ ሁሉን ፡ ትችላለህ
ችሎታህ ፡ ሳይለወጥ (፫x)
አቅምህም ፡ ሳይለወጥ (፫x)
ሁሉንም ፡ ታስተዳድራለህ
በፀጋህ ፡ ታስተዳድራለህ (፪x)
አመሰግንሃለሁ ፡ አመሰግንሃለሁ
አመሰግንሃለሁ ፡ አመሰግንሃለሁ (፪x)

ሰምተህ ፡ ዝም ፡ ማለት ፡ አታውቅም
ፀሎቴን ፡ አትንቅም
መቼ ፡ ሆኖልህ ፡ የእኔ ፡ ነገር
አቤት ፡ ጉድ ፡ ነው ፡ የአንተስ ፡ ፍቅር

ታዲያ ፡ እንደዚህ ፡ አድርገህልኝ
እንዴት ፡ ችዬ ፡ ዝም ፡ እላለሁ
ተነስቼ ፡ ለአንተ ፡ ጌታ ፡ ምሥጋናዬን ፡ አቀርባለሁ
እንዴት ፡ ዝም ፡ እላለሁ

አዝ፦ አንተ ፡ ገናና ፡ ሆይ ፡ ሁሉን ፡ ትገዛለህ
አንተ ፡ ገናና ፡ ሆይ ፡ ሁሉን ፡ ትችላለህ
ችሎታህ ፡ ሳይለወጥ (፫x)
አቅምህም ፡ ሳይለወጥ (፫x)
ሁሉንም ፡ ታስተዳድራለህ
በፀጋህ ፡ ታስተዳድራለህ (፪x)
አመሰግንሃለሁ ፡ አመሰግንሃለሁ
አመሰግንሃለሁ ፡ አመሰግንሃለሁ (፪x)