በገናውን (Begenawen) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 4.jpg


(4)

ይሆናል
(Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2003)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ፦ በገናውን እጄ ፡ እየደረደረ
አፌም ፡ ምህረትህን ፡ እየተናገረ
መንፈሴና ፡ ነፍሴ ፡ በአንድነት:ተስማምተው
ያመሰግኑሃል ፡ ጌታ ፡ ክበር ፡ ብለው ፡ ኦሆሆ
በምሥጋና ፡ የተፈራህ ፡ በአምልኮ ፡ ኦሆሆ
አምላኬ ፡ ሆይ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
(፪x)
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ

ተመስገን ፡ ሳልል ፡ መሰውያው ፡ ሳይከፈት
አፌ ፡ ሳይጠራህ ፡ ፀሐይ ፡ አትጠልቅም
ልኡል ፡ ነህ ፡ መልካም ፡ ሥምህ ፡ ያማረ
ዙፋንህ ፡ ከጥንት ፡ የተከበረ

አዝ፦ በገናውን እጄ ፡ እየደረደረ
አፌም ፡ ምህረትህን ፡ እየተናገረ
መንፈሴና ፡ ነፍሴ ፡ በአንድነት:ተስማምተው
ያመሰግኑሃል ፡ ጌታ ፡ ክበር ፡ ብለው ፡ ኦሆሆ
በምሥጋና ፡ የተፈራህ ፡ በአምልኮ ፡ ኦሆሆ
አምላኬ ፡ ሆይ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
(፪x)
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ

የገባኝ ፡ ነገር ፡ የተረዳሁት
ልቤ ፡ ውስጥ ፡ አለ ፡ ከአንተ ፡ ያገኘሁት
ዝም ፡ በል ፡ ቢሉኝ ፡ አይሆንልኝም
የገባኝ ፡ ፍቅርህ ፡ አያስችለኝም

አዝ፦ በገናውን እጄ ፡ እየደረደረ
አፌም ፡ ምህረትህን ፡ እየተናገረ
መንፈሴና ፡ ነፍሴ ፡ በአንድነት:ተስማምተው
ያመሰግኑሃል ፡ ጌታ ፡ ክበር ፡ ብለው ፡ ኦሆሆ
በምሥጋና ፡ የተፈራህ ፡ በአምልኮ ፡ ኦሆሆ
አምላኬ ፡ ሆይ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
(፪x)
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ

ያማረ ፡ ዜማ ፡ ነፍሴ ፡ አፈለቀች
ለአንተ ፡ ክብር ፡ ይሁን ፡ እያለች
እደሰታለሁ ፡ አምላኬ ፡ አንተ ፡ ነህ
ታማኙ ፡ ጌታ ፡ እንከን ፡ የሌለህ

አዝ፦ በገናውን እጄ ፡ እየደረደረ
አፌም ፡ ምህረትህን ፡ እየተናገረ
መንፈሴና ፡ ነፍሴ ፡ በአንድነት:ተስማምተው
ያመሰግኑሃል ፡ ጌታ ፡ ክበር ፡ ብለው ፡ ኦሆሆ
በምሥጋና ፡ የተፈራህ ፡ በአምልኮ ፡ ኦሆሆ
አምላኬ ፡ ሆይ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
(፪x)
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ
የለም ፡ እኮ ፡ ኧረ ፡ እንዳንተ ፡ የለም ፡ እኮ