ፍጥረት ፡ የሚደገፍበት (Fetret Yemidegefebet) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ:- ፍጥረት ፡ የሚደገፍበት
እኔም ፡ ተስፋ ፡ ማደርግበት
ጌታ ፡ ነው ፡ እንከን ፡ የሌለበት
ልዘምር ፡ እስቲ ፡ ልቀኝለት
ለሕይወት ፡ ጥያቂ ፡ ለእንቆቅልሹ
ጌታ ፡ ነው ፡ ምላሽ ፡ አቻ ፡ የለሹ
ሁሉንም ፡ መልካም ፡ ያደርገውና
ያስገርመናል ፡ ድንቅ ፡ ይሰራና
ያድንና (ኦሆሆሆሆ) ፤ ይባርክና (ኦሆሆሆሆ)
ሰው ፡ ያደርግና (ኦሆሆሆሆ) ፤ ያቆምና (ኦሆሆሆሆ)
ይደግፍና

እየባረኩኝ ፡ እባርክሃለሁ
በሕይወትህ ፡ ድንቅን ፡ አደርጋለሁ
ከአንተ ፡ ጋር ፡ ነኝ ፡ አትፍራ ፡ እንዳልከኝ
የኔ ፡ ጌታ ፡ ስንቱን ፡ አሳለፍከኝ
ስንት ፡ ጊዜ ፡ አዳንከኝ ፡ ከጥፋት
ልገልጽ ፡ አልችል ፡ የውለታህን ፡ ብዛት

ድንቅን ፡ አይቻለሁ ፡ ድንቅን ፡ አይቻለሁ
በሕይወት ፡ ዘመኔ ፡ ገና ፡ አመልክሃለሁ
ድንቅን ፡ አይቻለሁ ፡ ድንቅን ፡ አይቻለሁ
በሕይወት ፡ ዘመኔ ፡ እገዛልሃለሁ

አዝ:- ፍጥረት ፡ የሚደገፍበት
እኔም ፡ ተስፋ ፡ ማደርግበት
ጌታ ፡ ነው ፡ እንከን ፡ የሌለበት
ልዘምር ፡ እስቲ ፡ ልቀኝለት
ለሕይወት ፡ ጥያቂ ፡ ለእንቆቅልሹ
ጌታ ፡ ነው ፡ ምላሽ ፡ አቻ ፡ የለሹ
ሁሉንም ፡ መልካም ፡ ያደርገውና
ያስገርመናል ፡ ድንቅ ፡ ይሰራና
ያድንና (ኦሆሆሆሆ) ፤ ይባርክና (ኦሆሆሆሆ)
ሰው ፡ ያደርግና (ኦሆሆሆሆ) ፤ ያቆምና (ኦሆሆሆሆ)
ይደግፍና

ቁሻሻውን ፡ ታሪኬን ፡ ለውጠህ
ሰው ፡ አደረከኝ ፡ ኢየሱስ ፡ በእኔ ፡ ከብረህ
ገና ፡ ህጻን ፡ ሳለሁ ፡ የተሸከምከኝ
በጉያህ ፡ ውስጥ ፡ እስካሁን ፡ አለሁኝ
አልተውህም ፡ አልጥልህም ፡ ያልከኝ
ኢየሱሴ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ

ድንቅን ፡ አይቻለሁ ፡ ድንቅን ፡ አይቻለሁ
በሕይወት ፡ ዘመኔ ፡ ገና ፡ አመልክሃለሁ
ድንቅን ፡ አይቻለሁ ፡ ድንቅን ፡ አይቻለሁ
በሕይወት ፡ ዘመኔ ፡ እገዛልሃለሁ
(፪x)