ዓይኖቼ ወዳንተ ሲቀኑ (አይኖቼ ወዳንተ ሲቀኑ)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

። ዓይኖቼ ወዳንተ ሲቀኑ፥ ወዳንተ ሲቀኑ፥ ወዳንተ ሲቀኑ፣
። ኢየሱስ ቀናልኝ መንገዴ ብሩ ሆነ ቀኑ፤ ብሩህ ሆነ ቀኑ።

አንድ ችግር በመንገዴ እኔን ሲገጥመኝ፣
እዚያና እዚያ ስቅበዘበዝ መፍትሔ ላገኝ፣
ትዝ ትለኝና አንተን አስባለሁ፣
አይኖቼን ወዳንተ አቀናለሁ፤
ከችግሬም ቶሎ እፈታለሁ።
። ዓይኖቼ ወዳንተ ...

እመካብሀለሁ ጌታ ሁሉን ቻይ ነህ፣
የሚያስፈራራኝን ሁሉ ትሽራለህ፤
የጠላት ቀስቱንም ሰብረህ አይቻለሁ፣
ኤልሻዳይ አምላኬ እታመንሃለሁ፤
ዘላለም በቤትህ መኖር መርጫለሁ።