በፈረሰው ፡ ቅጥር ፡ ማን ፡ ይቆማል (Beferesew Qeter Man Yeqomal) - በረከት ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በረከት ፡ ተስፋዬ
(Bereket Tesfaye)

Bereket Tesfaye 1.jpeg


(1)

ሊቀ ፡ ካህኔ
(Liqe Kahenie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:23
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የበረከት ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Bereket Tesfaye)

የእግዚአብሔር ፡ ቤት ፡ ፈርሶ
መሠዊያው ፡ ተድበስብሶ
የእራስህን ፡ ቤት ፡ ትሰራለህ
ስለ ፡ ወንጌል ፡ አይገድህ

በፈረሰው ፡ ቅጥር ፡ ማን ፡ ይቆማል
ሁሉ ፡ የራሱን ፡ ድንጋይ ፡ ይክባል
በፈረሰው ፡ ቅጥር ፡ ማን ፡ ይቆማል
ኤሎሂ ፡ ማን ፡ ይሻለናል?

እግዚአብሔር ፡ ወይ ፡ ትውልድ ፡ አስነሳ
ስለ ፡ ቤትህ ፡ የሚሳሳ
ግድ ፡ የሚለው ፡ የወንጌል ፡ ነገር
በጥቅም ፡ የማይጭበረበር
ኤሎሂ (፫x) ፡ ፡ አሃ ፡ ኤሎሂ

የቀደሙት ፡ ሃዋሪያት ፡ ነቢያት
ራሳቸውን ፡ ሰጡ ፡ እስከሞት ፡ ድረስ
ዛሬ ፡ ራሱን ፡ ሚሰጥ ፡ ኧረ ፡ እርሱ ፡ ማነው
የወንጌሉ ፡ ቅናት ፡ ውስጡን ፡ የበላው

እግዚአብሔር ፡ ወይ ፡ ትውልድ ፡ አስነሳ
ስለ ፡ ቤትህ ፡ የሚሳሳ
ግድ ፡ የሚለው ፡ የወንጌል ፡ ነገር
በጥቅም ፡ የማይጭበረበር

ወንድም ፡ ለወንድሙ ፡ ማዘን ፡ ሲገባዉ
ባደባባይ ፡ ላይ ፡ ክስ ፡ ዝንተላዉ ፡ ምንድን ፡ ነው
እውነቱ ፡ ከተቀየረማ ፡ ከቀለላ ፡ ዋጋው ፡ ክርስትና
ምንድን ፡ ነው ፡ የሚሻለን ፡ ኤሎሂ ፡ መፍትሄ ፡ ስጠን

እግዚአብሔር ፡ ወይ ፡ ትውልድ ፡ አስነሳ
ስለ ፡ ወንድሙ ፡ የሚሳሳ
ግድ ፡ የሚለው ፡ የፍቅር ፡ ነገር
በውሸት ፡ የማይወነጅል
ኤሎሂ (፫x) ፡ አሃ ፡ ኤሎሂ

ትውልድ ፡ ሲተራመስ ፡ በራሱ ፡ መንገድ ፡ ላይ
ግማሹ ፡ ወደታች ፡ ግማሹ ፡ ወደላይ
ወዴት ፡ እንደምሄድ ፡ ትውልድ ፡ አላወቀም
የዛሬን ፡ እንጂ ፡ የነገን ፡ አላየም (፪x)

እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ ሰው ፡ አስነሳልን
መንገድህን ፡ የሚያሳየን
ቃልህን ፡ ብቻ ፡ የሚናገር
በሁኔታ ፡ የማይጭበረበር
ኤሎሂ (፬x)

የቀደሙት ፡ ሃዋሪያት ፡ ነቢያት
ራሳቸውን ፡ ሰጡ ፡ እስከሞት ፡ ድረስ
ዛሬ ፡ ራሱን ፡ ሚሰጥ ፡ ኧረ ፡ እርሱ ፡ ማነው
የወንጌሉ ፡ ቅናት ፡ ውስጡን ፡ የበላው

እግዚአብሔር ፡ ወይ ፡ ትውልድ ፡ አስነሳ
ስለ ፡ ቤትህ ፡ የሚሳሳ
ግድ ፡ የሚለው ፡ የወንጌል ፡ ነገር
በጥቅም ፡ የማይጭበረበር

እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ ሰው ፡ አስነሳልን
መንገድህን ፡ የሚያሳየን
ቃልህን ፡ ብቻ ፡ የሚናገር
በሁኔታ ፡ የማይጭበረበር
ኤሎሂ (፬x)

የእግዚአብሔር ፡ ቤት ፡ ፈርሶ ፣ መሠዊያው ፡ ተድበስብሶ
የእራስህን ፡ ቤት ፡ ትሰራለህ ፣ ስለ ፡ ወንጌል ፡ አይገድህ

በፈረሰው ፡ ቅጥር ፡ ማን ፡ ይቆማል
ሁሉ ፡ የራሱን ፡ ድንጋይ ፡ ይክባል
በፈረሰው ፡ ቅጥር ፡ ማን ፡ ይቆማል
ኤሎሂ ፡ ማን ፡ ይሻለናል?

እግዚአብሔር ፡ ወይ ፡ ትውልድ ፡ አስነሳ
ስለ ፡ ቤትህ ፡ የሚሳሳ
ግድ ፡ የሚለው ፡ የወንጌል ፡ ነገር
በጥቅም ፡ የማይጭበረበር
ኤሎሂ (፫x) ፡ አሃ ፡ ኤሎሂ
ኤሎሂ (፫x) ፡ አሃ ፡ ኤሎሂ