ተቀብሎኛል (Tekebelognal) - በረከት ፡ አለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በረከት ፡ አለሙ
(Bereket Alemu)

Bereket Alemu 1.jpg


(1)

ወዶ ፡ ዘማች
(Wedo Zemach)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፯ (2007)
ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 4:45
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የበረከት ፡ አለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Bereket Alemu)

ተቀብሎኛል (፰)
በሃምሳሉ ፡ አድርጎ ፡ የፈጠረኝ
የባህሪው ፡ ተካፋይ ፡ ያደረገኝ
በ ፡ በደል ፡ በ ፡ ሃጥያቴ
እንድጠፋ ፡ መች ፡ ወዶ
አላስችል ፡ ሲለው ፡ ከላይ
ይልቅ ፡ በ ፡ ፍቅር ፡ ወዶ

             ተቀብሎኛል (፬)

የመዳኔ ፡ ቀንድ ፡ ነው
የህወቴ ፡ መጀመሪያ
አዲስ ፡ ፍጥረት ፡ ያረገኝ
የኑሮዬ ፡ መመሪያ (፪)
አንተ ፡ የእኔ ፡ ነህ ፡ ብሎኛል
እኔም ፡ የርሱ ፡ ነኝ ፡ ብያለሁ
የኑሮዬ ፡ አጋር ፡ ያረኩት
ላልለየው ፡ ወደድኩት (፪)

            የወደደኝ ፡ እኔን ፡ ጠራኝ
            የጠራኝ ፡ ፍጹም ፡ አጸደቀኝ
            ጸድቂአለሁ ፡ ቃሉ ፡ አክብሮኛል
            ሰማያዊ ፡ ዘጋ ፡ አድርጎኛል
            ሆ
            የወደደኝ ፡ እኔን ፡ ጠራኝ
            የጠራኝ ፡ ፍጹም ፡ አጸደቀኝ
            ጸድቂአለሁ ፡ ቃሉ ፡ አክብሮኛል
            ሰማያዊ ፡ ዘጋ ፡ አድርጎኛል
            ሆ
ልጄ ፡ ሲለኝ ፡ (አያፍርም)
የኔ ፡ ሲለኝ ፡ (አያፍርም) (፬)
ለምንድነው ፡ ያላፈረብኝ
ስለማላሳፍረው (፬)
ለምንድነው ፡ ያላፈረብህ
ስለማታሳፍረው (፮)
ለምንድነው ፡ ያላፈረብሽ
ኪዲ ፦ ስለማላሳፍረው (፬)
ስለማናሳፍረው (፰)