በስግደት (Besigdet) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Lyrics.jpg


(5)

በመጀመሪያ ፡ እግዚአብሔር
(Bemejemeria Egziabhier)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:49
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

በስግደት ፡ በአምልኮ ፡ በብዙ ፡ ምሥጋና ፡
በዕውነት ፡ በመንፈስ ፡ ፊትህ ፡ ልምጣና ፡
ላምልክህ ፡ እንደገና (፫)

እንደወራጅ ፡ ዉሃ ፡ ልክ ፡ እንደጅረቱ
አይቋረጥብህ ፡ አምልኮዬ ፡ ፊቱ
ይፍሰስ ፡ በማለዳው ፡ ይፍሰስ ፡ በሌሊቱ
መሳይ ፡ ስለሌለው ፡ ጌታ ፡ ጌትነቱ (፪)

ላምልከው ፡ በአምልኮዬ ፡
ላክብረው ፡ በዝማሬዬ
ላግንነው ፡ በዕልልታዬ ፡
ላድምቀው ፡ በጭብጨባዬ
ይገባዋል ፡ እና ፡ ጌታዬ (፬)

የመውደዴን ፡ ልኩን ፡ የፍቅሬን ፡ መግልጫ
ካለኝ ፡ ነገር ፡ ሁሉ ፡ የምሰጠው ፡ ብልጫ
ለሕይወቴ ፡ ጌታ ፡ ለነፍሴ ፡ ንጉሥ
አለኝ ፡ የምሰዋው ፡ ከነፍሴ ፡ የሚፈስ

የቅኔው ፡ የዜማ ፡ ሽታ ፡ ታጅቦ ፡ በብዙ ፡ ሆታ
ከምድር ፡ ይውጣ ፡ ያስተጋባ ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ ማደሪያ ፡ ይግባ
ይገባሃል ፡ እና ፡ ጌታዬ (፬)

በስግደት ፡ በአምልኮ ፡ በብዙ ፡ ምሥጋና ፡
በዕውነት ፡ በመንፈስ ፡ ፊትህ ፡ ልምጣና ፡
ላምልክህ ፡ እንደገና (፫)