ኧረ ፡ አይጥልም (Ere Aytelem) - አገኘሁ ፡ ይደግ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አገኘሁ ፡ ይደግ
(Agegnehu Yideg)

Agegnehu Yideg 7.jpg


(7)

አልበም
(Chelemayie Bera)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2012)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአገኘሁ ፡ ይደግ ፡ አልበሞች
(Albums by Agegnehu Yideg)

ያድነኛል : ብዬ : ፊቱን : ተማፅኜ
ወድቄ : አልቀረሁም : ጌታን : ተሜምኜ
ያድነኛል : ብዬ : ደጁን : ተማፅኜ
ወድቄ : አልቀረሁም : ጌታን : ተሜምኜ

ስለቴን : ልክፈል : ምስጋና : ላምጣ
የነፉሴ : መስዋት : ወደላይ : ይውጣ
መች : ቀረሁ : እኔ : እንዳለቀስኩ
ተራዬ : ደርሶ : በእርሱ : ታሰብኩኝ

ኧረ : አይጥልም : እግዚአብሔር : አይጥልም
ኧረ : አይጥልም : በፍፁም : አይጥልም (2)

በመከራ : ቀን : መሸሸጊያ : ነው : የሚታመኑትን : ያውቃል
ተመልሶ : ይራራል : እንጂ : በልኩ : መች : ያስጨንቃል (2)

ነፋሱ : ሄደ : ወጀብ : ፀጥ : አለ
ሸክሙ : ከላዬ : ተንከባለለ
ተራራው : ሆነ : ደልዳላ : ሜዳ
እግዚአብሔር : ደርሶ : ልጁን : ረዳ

ኧረ : አይጥልም : እግዚአብሔር : አይጥልም
ኧረ : አይጥልም : በፍፁም : አይጥልም
ኧረ : አይጥልህም : እግዚአብሔር : አይጥልህም
ኧረ : አይጥልሽም : በፍፁም : አይጥልሽም

በመከራ : ቀን : መሸሸጊያ : ነው : የሚታመኑትን : ያውቃል
ተመልሶ : ይራራል : እንጂ : በልኩ : መች : ያስጨንቃል (2)

ምድረበዳዬን : አለመለመ
በውብ : ድንጋዮች : ፊቴን : ሸፈነ
በከፍታ : ላይ : እግሬን : አፀና
የሰይጣን : አሳብ : ቀረበት : መና

ኧረ : አይጥልም : እግዚአብሔር : አይጥልም
ኧረ : አይጥልም : በፍፁም : አይጥልም
ኧረ : አይጥልህም : እግዚአብሔር : አይጥልህም
ኧረ : አይጥልሽም : በፍፁም : አይጥልሽም

በመከራ : ቀን : መሸሸጊያ : ነው : የሚታመኑትን : ያውቃል
ተመልሶ : ይራራል : እንጂ : በልኩ : መች : ያስጨንቃል (2)

ይገባውን : ተስፋ : መቼ : ይረሳል
በጊዜው : ደርሶ : እንባን : ያብሳል
እርሱ : ሰው : አይደል : አይለወጥም
ርስቱን : ለጠላት : ፈፅሞ : አይሰጥም

ኧረ : አይጥልም : እግዚአብሔር : አይጥልም
ኧረ : አይጥልም : በፍፁም : አይጥልም
ኧረ : አይጥልህም : እግዚአብሔር : አይጥልህም
ኧረ : አይጥልሽም : በፍፁም : አይጥልሽም

በመከራ : ቀን : መሸሸጊያ : ነው : የሚታመኑትን : ያውቃል
ተመልሶ : ይራራል : እንጂ : በልኩ : መች : ያስጨንቃል (2)