እውነተኛ ፡ አምልኮ (Ewnetegna Amleko) - ዜማ ፡ ለክርስቶስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዜማ ፡ ለክርስቶስ
(Zema 4 Christ)

Zema 4 Christ 2.jpg


(2)

ክቡር ፡ ቀን
(Kebur Qen)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2013)
ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 4:12
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዜማ ፡ ለክርስቶስ ፡ አልበሞች
(Albums by Zema 4 Christ)

አመጣጤም ፡ ባያምርም ፡ እግዚአብሔር ፡ ይወደኛል
አኗኗሬም ፡ ባያምርም ፡ እግዚአብሔር ፡ ይወደኛል
አፍቃሪ ፡ ባይኖረኝም ፡ እርሱ ፡ ግን ፡ ይወደኛል
ወላጆች ፡ ባይኖሩኝም ፡ እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ ማለቢ. (1) .

ወላጆች ፡ ባይኖሩትም ፡ አመጣጧ ፡ ባያምርም
ልጆች ፡ ግን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ስጦታ ፡ ናቸው
እነሱን ፡ ተንከባክቦ ፡ በፍቅር ፡ ማሳደግ
የአምላክን ፡ ስጦታ ፡ ማክበር ፡ ነው

ንጹህ ፡ የሆነ ፡ ነውር ፡ አልባ
ጌታን ፡ የሚያስከብር ፡ አምልኮ
እውነተኛ ፡ የሆነ ፡ አገልግሎት
በእግዚአብሔር ፡ አብ ፡ ዘንድ ፡ ይሄ ፡ ነው

አፍቃሪ ፡ ባይኖረውም ፡ አኗኗሯ ፡ ባያምርም
እግዚአብሔር ፡ በልጆጅ ፡ ላይ ፡ አላማ ፡ አለው
ፍቅር ፡ እያሳዩ ፡ እነሱን ፡ ማሳደግ
የጌታን ፡ አላማ ፡ ከግብ ፡ ማድረስ ፡ ነው

ንጹህ ፡ የሆነ ፡ ነውር ፡ አልባ
ጌታን ፡ የሚያስከብር ፡ አምልኮ
እውነተኛ ፡ የሆነ ፡ አገልግሎት
በእግዚአብሔር ፡ አብ ፡ ዘንድ ፡ ይሄ ፡ ነው (፪x)