የማንነህ (Yemaneh) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 3.jpg


(3)

ዝምታው
(Zemetaw)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

በመስቀሉ ፡ ገለጠ ፡ የፍቅሩን ፡ ዳርቻ
ልጀነትን ፡ አገኘሁ ፡ በማመኔ ፡ ብቻ
ላልሰሙ ፡ ልንገራቸው ፡ የማን ፡ ነህ ፡ ቢሉኝ
ደም ፡ የተከፈለልኝ ፡ የኢየሱስ ፡ ነኝ

እንድኖር ፡ በኩኔ ፡ በድካሜ ፡ አንገት ፡ እንድደፋ
የጠላቴ ፡ አላማው ፡ ቢሆንለት ፡ እንዳይኖረኝ ፡ ተስፋ
ኢየሱስ ፡ ጠበቃዬ ፡ ቀና ፡ አረገኝ ፡ በደሙ ፡ አንጽቶ
በድል ፡ እራመዳለሁ ፡ ሰንሰለቴ ፡ በኢየሱስ ፡ ተፈትቶ

በወንጌሉ ፡ እውነት ፡ ነጻ ፡ አውጥቶ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
ፍርድና ፡ ኩነኔ ፡ የሊለበኝ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
በነጻነት ፡ ልኖር ፡ ነጻ ፡ አውጥቶ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
ተደላድያለሁ ፡ ሰላሜ ፡ በዝቶ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
የጌታ ፡ ነኝ ፡ የጌታ ፡ ነኝ ፡ የጌታ ፡ ነኝ ፡ የጌታ ፡ ነኝ

ከሳሼም ፡ መጣ ፡ ሎሴ ፡ ጠርዞ
ማኅተም ፡ አትሞ ፡ ማስረጃውን ፡ ይዞ
ፈራጄ ፡ ኢየሱስ ፡ ደሙ ፡ ነበረ
ጠላቴም ፡ ሸሸ ፡ እየደነበረ

የማን ፡ ነህ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
የማን ፡ ነህ ፡ የጌታ ፡ ነኝ

በመስቀሉ ፡ ገለጠ ፡ የፍቅሩን ፡ ዳርቻ
ልጀነትን ፡ አገኘሁ ፡ በማመኔ ፡ ብቻ
ላልሰሙ ፡ ልንገራቸው ፡ የማን ፡ ነህ ፡ ቢሉኝ
ደም ፡ የተከፈለልኝ ፡ የኢየሱስ ፡ ነኝ

ክእንግዲህ ፡ ወስኛለሁ ፡ በእርሱ ፡ በቻ ፡ ሕይወቴ ፡ እንዲመካ
ሁሉን ፡ አሸንፋለሁ ፡ የሚረዳኝ ፡ አለ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
ወገቤን ፡ ታጥቂያለሁ ፡ በመንፈሱ ፡ ኃይል ፡ ተሞልቼ
ወደፊት ፡ እሄዳለሁ ፡ ያለፈውን ፡ የኋላዬን ፡ ትቼ

በወንጌሉ ፡ እውነት ፡ ነጻ ፡ አውጥቶ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
ፍርድና ፡ ኩነኔ ፡ የሊለበኝ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
በነጻነት ፡ ልኖር ፡ ነጻ ፡ አውጥቶ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
ተደላድያለሁ ፡ ሰላሜ ፡ በዝቶ ፡ ገዝቶኛል ፡ በደሙ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
የጌታ ፡ ነኝ ፡ የጌታ ፡ ነኝ ፡ የጌታ ፡ ነኝ ፡ የጌታ ፡ ነኝ

ከሳሼም ፡ መጣ ፡ ሎሴ ፡ ጠርዞ
ማኅተም ፡ አትሞ ፡ ማስረጃውን ፡ ይዞ
ፈራጄ ፡ ኢየሱስ ፡ ደሙ ፡ ነበረ
ጠላቴም ፡ ሸሸ ፡ እየደነበረ

የማን ፡ ነህ ፡ የጌታ ፡ ነኝ
የማን ፡ ነህ ፡ የጌታ ፡ ነኝ