እጄን ፡ አነሳሁ (Ejien Anesaw) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 3.jpg


(3)

ዝምታው
(Zemetaw)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 7:15
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

የልቤን ፡ ማዋየው ፡ የውስጤን ፡ ሚስጥረኛዬ
ባዝንም ፡ ብከፋም ፡ ማይለየኝ ፡ መጽናኛዬ
ነፍሴ ፡ ትረካለች ፡ በአንደበቱ ፡ ቃል ፡ በምክሩ
የመኖሬ ፡ ትርጉም ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ሚስጥሩ

ወደ ፡ አባቴ ፡ ልቅረብ ፡ እንጂ
የሚረዳኝ ፡ የለም ፡ ከእርሱ ፡ ውጪ
ወደ ፡ አባቴ ፡ ልቅረብ ፡ እንጂ
የሚረዳኝ ፡ የለም ፡ ከእርሱ ፡ ውጪ

እጄን ፡ አነሳሁ ፡ ወደ ፡ ላይ
ወደ ፡ ሚሰማኝ ፡ ወደሚያይ
ጩኸቴን ፡ ሰምቶ ፡ ይመልሳል
እንባዬን ፡ ከዓይኔ ፡ ያብሳል
አባትዬ ፡ አባትዬ ፡ አባብዬ

ከእስትንፋሴ ፡ ይልቅ ፡ ይቀርበኛል ፡ አይርቀኝም
የፍቅር ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ ገብቶልኛል ፡ አይተወኝም
እንዳወራው ፡ ድፍረት ፡ ይሰጠኛል ፡ የፍቅር ፡ ዓይኖቹ
ልቤ ፡ ተፈወሰ ፡ ሲዳስሰኝ ፡ በመልካም ፡ እጆቹ

መልካም ፡ ነህ ፡ መልካም ፡ መልካም ፡ ነህ
መልካም ፡ ነህ ፡ መልካም ፡ መልካም ፡ ነህ

የልቤን ፡ ማዋየው ፡ የውስጤን ፡ ሚስጥረኛዬ
ባዝንም ፡ ብከፋም ፡ ማይለየኝ ፡ መጽናኛዬ
ነፍሴ ፡ ትረካለች ፡ በአንደበቱ ፡ ቃል ፡ በምክሩ
የመኖሬ ፡ ትርጉም ፡ እርሱ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ሚስጥሩ

ወደ ፡ አባቴ ፡ ልቅረብ ፡ እንጂ
የሚረዳኝ ፡ የለም ፡ ከእርሱ ፡ ውጪ
ወደ ፡ አባቴ ፡ ልቅረብ ፡ እንጂ
የሚረዳኝ ፡ የለም ፡ ከእርሱ ፡ ውጪ

እጄን ፡ አነሳሁ ፡ ወደ ፡ ላይ
ወደ ፡ ሚሰማኝ ፡ ወደሚያይ
ጩኸቴን ፡ ሰምቶ ፡ ይመልሳል
እንባዬን ፡ ከዓይኔ ፡ ያብሳል
አባትዬ ፡ አባትዬ ፡ አባብዬ

ትዋሽ ፡ ዘንድ ፡ እንደሰው ፡ አይደለህ ፡ እውነተኛ ፡ ነህ
የተናገርከውን ፡ ታደርጋለህ ፡ ትፈጽማለህ
ቢታመኑህ ፡ ታማኝ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ወረት ፡ የሌለህ
ከአጠገቤ ፡ ሁሌ ፡ ማትለየኝ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ነህ

መልካም ፡ ነህ ፡ መልካም ፡ መልካም ፡ ነህ
መልካም ፡ ነህ ፡ መልካም ፡ መልካም ፡ ነህ

ትልቅነትህ ፡ እየገረመኝ
አጠገቤ ፡ ነህ ፡ ይሄም ፡ ሲደንቀኝ
ዘልቀህ ፡ ውስጤ ፡ ገብተሃል
መኖሪያህን ፡ አድርገሃል
የእኔ ፡ ሆነሃል