ኑሮዬ ፡ በኪዳን ፡ ነው (Nuroyie Bekidan New) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 1.jpg


(1)

ኑሮዬ ፡ በኪዳን ፡ ነው
(Nuroyie Bekidan New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

 
ሃገር ፡ ምድር ፡ ሲናወጥ ፡ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ሲታገል ፡ ለማምለጥ
እየባሰ ፡ ግር ፡ ግሩ ፡ ሕይወቴን ፡ ሊረብሽ ፡ ሊያስፈሩ
ለካ ፡ ቆሜ ፡ ሳስበው ፡ ኑሮዬ ፡ በኪዳን ፡ ነው
ኧረ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ ያለው ፡ እርሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

አዝ፦ ኪዳን ፡ አለኝ ፡ የእውነትም ፡ ቃል ፡ አለኝ
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ልጁ ፡ ያደረገኝ
መመኪያዬ ፡ የእውነትም ፡ ተስፋዬ
እርሱ ፡ ላይ ፡ ነው ፡ መደገፊያዬ (፪x)

እንድጠፋ ፡ ፈልጐ ፡ ያ ፡ ክፉ ፡ ሊወጠኝ ፡ ሲጥር
አልገባውም ፡ መሰለኝ ፡ እንዳለኝ ፡ ሃይለኛ ፡ ቅጥር
ሕይወቴን ፡ ሊተናኮል ፡ ጠጋ ፡ ጠጋ ፡ ሲለኝ
ኪዳኑን ፡ የሚያከብረው ፡ እግዚአብሔር ፡ ወጣልኝ

እስኪ ፡ በል ፡ ተናገር ፡ አሉኝ
እንዴት ፡ ነው ፡ ሚረዳህ ፡ አሉኝ
ልናገር ፡ አፌን ፡ ሞልቼ
የመጣውን ፡ ከአባቶቼ
ያኔም ፡ አሁንም ፡ ይሰራል
አልፎም ፡ ያድነኛል
የተጻፈውን ፡ ሳምን ፡ የቃልኪዳኑን (፪x)

አዝ፦ ኪዳን ፡ አለኝ ፡ የእውነትም ፡ ቃል ፡ አለኝ
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ልጁ ፡ ያደረገኝ
መመኪያዬ ፡ የእውነትም ፡ ተስፋዬ
እርሱ ፡ ላይ ፡ ነው ፡ መደገፊያዬ

በሕይወቴ ፡ ስፈራ ፡ ነገ ፡ ስለሚሆነው ፡ ሳላቅ
ነገ ፡ ስለሚሆነው ፡ አለኝ ፡ ተው ፡ አትጨነቅ
በነጻነት ፡ እንድትኖር ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ ነኝ ፡ አለኝ
ይሄ ፡ የእውነት ፡ ኪዳን ፡ እንዳልሰጋ ፡ አረገኝ

አዝ፦ ኪዳን ፡ አለኝ ፡ የእውነትም ፡ ቃል ፡ አለኝ
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ልጁ ፡ ያደረገኝ
መመኪያዬ ፡ የእውነትም ፡ ተስፋዬ
እርሱ ፡ ላይ ፡ ነው ፡ መደገፊያዬ

እስኪ ፡ በል ፡ ተናገር ፡ አሉኝ
እንዴት ፡ ነው ፡ ሚረዳህ ፡ አሉኝ
ልናገር ፡ አፌን ፡ ሞልቼ
የመጣውን ፡ ከአባቶቼ
ያኔም ፡ አሁንም ፡ ይሰራል
አልፎም ፡ ያድነኛል
የተጻፈውን ፡ ሳምን ፡ የቃልኪዳኑን (፪x)

አለኝ ፡ ቃልኪዳን ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ
አለኝ ፡ ቃልኪዳን ፡ እንዴት ፡ ልፈራ (፰x)