አያለሁ (Ayalehu) - ዮሴፍ ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ ካሳ
(Yosef Kassa)

Yosef Kassa 1.jpg


(1)

ኑሮዬ ፡ በኪዳን ፡ ነው
(Nuroyie Bekidan New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Yosef Kassa)

የውስጤ ፡ የእኔ ፡ ፍላጐቴ
ክብርህ ፡ ነው ፡ የሁሌ ፡ ጥማቴ
ለሃገር ፡ ለወገን ፡ መፍትሄ ፡ ስንሆን
የተወሰድብን ፡ ሲመለስልን
ይሄ ፡ ነው ፡ ጥማቴ ፡ የውስጤ ፡ ርሃቤ
ይህንን ፡ አያለሁ ፡ አምኖሃል ፡ ልቤ

የቤትህ ፡ ስርአት ፡ ተበላሽቶ
ተው ፡ የሚል ፡ የሚመልሰን ፡ ጠፍቶ
ይህ ፡ ሁሉ ፡ አካሄድ ፡ ያቆምና
አያለሁ ፡ ታድሶ ፡ እንደገና

አዝ፦ አያለሁ ፡ ክብርህ ፡ ቤትህን ፡ ሞልቶ
አያለሁ ፡ ያዘነው ፡ ተጽናንቶ
አያለሁ ፡ የፈረሰው ፡ ቅጥር
አያለሁ ፡ ታድሶ ፡ በክብር
አያለሁ ፡ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ሲገረም
አያለሁ ፡ ትንቢቱም ፡ ሲፈጸም

ከጥንቱ ፡ የነበረው ፡ ሃይልህ
ለትውልድ ፡ መፍትሄ ፡ የነበርህ
አያለሁ ፡ የአንተ ፡ ክብር ፡ ሲያበራ
በእጥፍ ፡ በዚህ ፡ ዘመን ፡ ሲሰራ

አዝ፦ አያለሁ ፡ ክብርህ ፡ ቤትህን ፡ ሞልቶ
አያለሁ ፡ ያዘነው ፡ ተጽናንቶ
አያለሁ ፡ የፈረሰው ፡ ቅጥር
አያለሁ ፡ ታድሶ ፡ በክብር
አያለሁ ፡ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ሲገረም
አያለሁ ፡ ትንቢቱም ፡ ሲፈጸም

ሕይወቱ ፡ ኑሮው ፡ የጨላለመ
በሃዘን ፡ ልቡ ፡ የደካከመ
አያለሁ ፡ የአንተ ፡ ክብር ፡ ሲመጣ
ጥያቄ ፡ ነገር ፡ ሁሉ ፡ ሲፈታ

አዝ፦ አያለሁ ፡ ክብርህ ፡ ቤትህን ፡ ሞልቶ
አያለሁ ፡ ያዘነው ፡ ተጽናንቶ
አያለሁ ፡ የፈረሰው ፡ ቅጥር
አያለሁ ፡ ታድሶ ፡ በክብር
አያለሁ ፡ ሰው ፡ ሁሉ ፡ ሲገረም
አያለሁ ፡ ትንቢቱም ፡ ሲፈጸም