ዘመን ፡ መጣ (Zemen Meta) - ዮሴፍ ፡ በቀለ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሴፍ ፡ በቀለ
(Yoseph Bekele)

Lyrics.jpg


(3)

ስንቱን ፡ ላውራ
(Sentun Lawra)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሴፍ ፡ በቀለ ፡ አልበሞች
(Albums by Yoseph Bekele)

ገመዴ ፡ ባማረ ፡ ውብ ፡ ስፍራ ፡ ወደቀችልኝ (፪x)
እርስቴም ፡ በእርሱ ፡ በኢየሱሴ ፡ ተዋበችልኝ (፪x)
እፎይ ፡ አሰኘኝ ፡ ጌታ ፡ ቤቴ ፡ ገብት
መራራ ፡ የሆነውን ፡ ታሪኬን ፡ ለውጦ
(፪x)

አዝ፦ መጐብኛዬ ፡ ዘመን ፡ መጣ
ቀን ፡ ወጣልኝ ፡ በዚህ ፡ ጌታ
አርፌያለሁ ፡ በዓለቱ ፡ ላይ
ሲደርስልኝ ፡ ጌታ ፡ ከላይ
ጌታ ፡ ከላይ ፡ ከላይ (፬x)

በምድረበዳ ፡ ውስጥ ፡ ከአለት ፡ ውኃ ፡ አፍልቆ
እኔን ፡ አረካልኝ ፡ መገፋቴን ፡ አይቶ
የዘመናት ፡ ለቅሶ ፡ እምባ ፡ ታበሰልኝ
ልዑል ፡ ከዙፋኑ ፡ ለእኔ ፡ ሲነሳልኝ
ምሥጋና ፡ አሄ ፡ ምሥጋና ፡ አሄ ፡ አሄ
ምሥጋና ፡ አሄ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ
አምልኮ ፡ አሄ ፡ አምልኮ ፡ አሄ ፡ አሄ
አምልኮ ፡ አሄ ፡ ለኢየሱስ ፡ ጌታዬ
ኢየሱስ ፡ ጌታዬ (፬x)

አዝ፦ መጐብኛዬ ፡ ዘመን ፡ መጣ
ቀን ፡ ወጣልኝ ፡ በዚህ ፡ ጌታ
አርፌያለሁ ፡ በዓለቱ ፡ ላይ
ሲደርስልኝ ፡ ጌታ ፡ ከላይ
ጌታ ፡ ከላይ ፡ ከላይ (፬x)

መጐብኛዬ ፡ ጊዜው ፡ ዘመን ፡ መጥቶልኛል
የሃዘኑ ፡ ጊዜ ፡ አልፎ ፡ ደስታ ፡ ቤቴ ፡ ሞልቷል
ጠላት ፡ ዐይኑ ፡ እያየ ፡ ይሄው ፡ ጉብኝቴ
አከናወነልኝ ፡ ሁሉንም ፡ አባቴ
ምሥጋና ፡ አሄ ፡ ምሥጋና ፡ አሄ ፡ አሄ
ምሥጋና ፡ አሄ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ
ዝማሬ ፡ አሄ ፡ ዝማሬ ፡ አሄ ፡ አሄ
ዝማሬ ፡ አሄ ፡ ለኢየሱስ ፡ ጌታዬ
ኢየሱስ ፡ ጌታዬ (፮x)