የልቤ ፡ ደስታ (Yelebie Desta) - ዮሐንስ ፡ ግርማ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ ግርማ
(Yohannes Girma)

Lyrics.jpg


(2mro)

እርስቴ ፡ ነህ
(Erestie Neh)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ ግርማ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Girma)

አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ
የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ
በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ
ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x)

ምንም ፡ በሌለበት ፡ ማይነጥፍ ፡ ደስታ
ብር ፡ ያልደጋገፈው ፡ የዚህ ፡ አለም ፡ ስጦታ
ፊትን ፡ የሚያበራ ፡ ከላይ ፡ የሆነው
ዘላቂው ፡ ደስታዬ ፡ ጌታ ፡ ባንተ ፡ እኮ ፡ ነው

አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ
የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ
በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ
ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x)

አይኖቼን ፡ ወደ ፡ ተራሮች ፡ ባነሳ
መመኪያን ፡ ለማግኘት ፡ ለእኔ ፡ የሚሳሳ
ለአይን ፡ የሚሞላ ፡ ከቶ ፡ አንድም ፡ አላየሁ
ይልቅ ፡ ባንተ ፡ ሆነ ፡ ልቤን ፡ ደስ ፡ የሚለው

አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ
የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ
በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ
ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x)

በስደት ፡ ምድር ፡ ላይ ፡ በደረቅ ፡ በረሃ
ለአይን ፡ ተስፋ ፡ ሳይኖር ፡ ለጥም ፡ የሚሆን ፡ ውሃ
ዙሪያ ፡ ሲጨላልም ፡ መጽናናት ፡ ሲሳነኝ
በእንግድነት ፡ ሀገር ፡ ስራህ ፡ መዝሙር ፡ ሆነኝ

አዝ፦ የልቤ ፡ ደስታ ፡ ጌታ
የልቤ ፡ ደስታ ፡ የሱስ
በገናዬን ፡ ልያዝ ፡ ልቀኝልህ
ነፍሴ ፡ ውላ ፡ ታድራለች ፡ በስምህ (፪x)