ከሰማያት ፡ በላይ (Kesemayat Belay) - ዮሐንስ ፡ ግርማ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ ግርማ
(Yohannes Girma)

Yohannes Girma 2.jpg


(2)

እርስቴ ፡ ነህ
(Erestie Neh)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 4:49
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ ግርማ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Girma)

ሠማይን ፡ ዘርግተህ ፡ እንዲህ ፡ አንጣለሃል
ከትልቅነቱ ፡ ብዛት ፡ የሰው ፡ ስሌት ፡ ያልፋል
አንተ ፡ የሰራኸው
በስንዝር ፡ የለካኸው
ይህ ፡ ሰማይ ፡ ትልቅ ፡ ከተባለ
ሰሪው ፡ ምን ፡ ትባላለህ (#3)

አዝ፦ ከሰማያት ፡ በላይ ፡ በላይ
ከምድርም ፡ በላይ ፡ በላይ
ከፍጥረታት ፡ በላይ ፡ በላይ
አንት ፡ ትልቅ ፡ ነህ
አንት ፡ ትልቅ ፡ ነህ (፫x)

በምድር ፡ የሰው ፡ ቁጥር ፡ እጅጉን ፡ ብዙ ፡ ነው
ከአዳም ፡ ጀምሮ ፡ እስካሁን ፡ የኖረው
በፊት ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ ሲታይ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
በገንቦ ፡ እንዳለች ፡ ትንሽ ፡ ጠብታ
ምትገርም ፡ ነህ ፡ ጌታ

አዝ፦ ከሰማያት ፡ በላይ ፡ በላይ
ከምድርም ፡ በላይ ፡ በላይ
ከፍጥረታት ፡ በላይ ፡ በላይ
አንት ፡ ትልቅ ፡ ነህ
አንት ፡ ትልቅ ፡ ነህ (፫x)

በምድር ፡ ለሚኖሩ ፡ ምድር ፡ ሰፊ ፡ እርስት ፡ ናት
ስፋቷን ፡ በብዙ ፡ ቁጥር ፡ የሚያሰሏት
አንተ ፡ ግን ፡ ጌታዬ ፡ ትልቅ ፡ ትልቅ ፡ ነህ
በክበቦቿ ፡ ላይ ፡ ትቀመጣለህ
ከፍ ፡ ከፍ ፡ ላድርግህ

አዝ፦ ከሰማያት ፡ በላይ ፡ በላይ
ከምድርም ፡ በላይ ፡ በላይ
ከፍጥረታት ፡ በላይ ፡ በላይ
አንት ፡ ትልቅ ፡ ነህ
አንት ፡ ትልቅ ፡ ነህ (፭x)