እግዚአብሔር ፡ አለ (Egziabhier Ale) - ወርቅነህ ፡ አላሮ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ወርቅነህ ፡ አላሮ
(Workneh Alaro)

Workneh Alaro 1.jpg


(1)

ከእሳት ፡ ውስጥ ፡ የነጠቀኝ
(Kesat West Yeneteqegn)

ዓ.ም. (Year): ዓ.ም. (Year)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የወርቅነህ ፡ አላሮ ፡ አልበሞች
(Albums by Workneh Alaro)

የአብርሃም ፡ የይስሃቅ ፡ የያዕቆብ ፡ አምላክ
ዛሬም ፡ በቅዱስ ፡ ማደሪያው ፡ አለና
ሥጋ ፡ ለባሽ ፡ ሁሉ ፡ በፊቱ ፡ ዝም ፡ ይበል
እግዚአብሔር ፡ አለና

አዝ፦ የምድር ፡ ዳርቻ ፡ ፈጣሪ
ለዘለዓለምም ፡ ነዋሪ
ማይደክም ፡ ማይታክተዉ
ማስተዋሉ ፡ ማይመረመረዉ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በከፍታው

ለደካማ ፡ ኃይልን ፡ ይሰጣል
ጉልበት ፡ ላጣው ፡ ብርታት ፡ ይጨምራል
በጽድቁ ፡ ቀን ፡ ደግፎ ፡ ይይዛል
እግዚአብሔር ፡ ህዝቡን ፡ መቼ ፡ ይተዋል (፪x)

አዝ፦ የምድር ፡ ዳርቻ ፡ ፈጣሪ
ለዘለዓለምም ፡ ነዋሪ
ማይደክም ፡ ማይታክተዉ
ማስተዋሉ ፡ ማይመረመረዉ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በከፍታው

ወፎችን ፡ በእፍኙ ፡ የሰፈረ
ሠማይን ፡ በስንዝር ፡ የለካዉ
ከፍ ፡ ባለ ፡ ዙፋን ፡ ላይ ፡ የተቀመጠው
ለትውልድ ፡ ሁሉ ፡ መጠጊያ ፡ ነው

አዝ፦ የምድር ፡ ዳርቻ ፡ ፈጣሪ
ለዘለዓለምም ፡ ነዋሪ
ማይደክም ፡ ማይታክተዉ
ማስተዋሉ ፡ ማይመረመረዉ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በከፍታው

ስለድሆች ፡ መከራ ፡ ስለችግረኞች
ጌታዬ ፡ ይመጣል ፡ ወደመቅደሱ ፡ በድንገት
የወደቀ ፡ ይነሳል ፡ የሳተ ፡ ይመለሳል
በእግዚአብሔር ፡ ጉብኝት ፡ ገና ፡ ጠላት ፡ ይቃጠላል

ተስፋ ፡ የቆረጣችሁ ፡ በእምነት ፡ ደክማችሁ
በጠላትም ፡ ዛቻ ፡ አንገት ፡ የደፋቹህ
አምላካቹህ ፡ በበቀል ፡ በእርግጥ ፡ ይመጣል
የእናንተም ፡ ደስታ ፡ ገናስ ፡ ከሩቁ ፡ ይሰማል

ያዕቆብ ፡ ሆይ ፡ እስራኤልም ፡ ሆይ
አልሰማህም ፡ ወይ ፡ አላወቅክም ፡ ወይ (፪x)
መንግዴ ፡ ከእግዚአብሔር ፡ ተሰውራለች
ፍርዴም ፡ ከአምላኬ ፡ ደግሞም ፡ አልፋለች
ለምን ፡ ትላለህ ፡ ለምንስ ፡ እንዲህ ፡ ትናገራለህ
አልሰማህም ፡ ወይ ፡ አላወክህም ፡ ወይ

የእኛ ፡ ጌታ ፡ አለ ፡ (አለ) ፡ እንደነገሠ ፡ (አለ)
አላረጀም ፡ (አለ) ፡ አልደከመም ፡ (አለ)
አይታክትም ፡ (አለ) ፡ አለ ፡ ጌታ ፡ (አለ)
አለ ፡ ጌታ ፡ (አለ) ፡ ትናንትናም ፡ ዛሬም ፡ (አለ)
ነገም ፡ ለዘለዓለም ፡ (አለ) ፡ ያው ፡ ነው ፡ ኢየሱስ (አለ)
አለ ፡ ጌታ ፡ (አለ) ፡ አለ ፡ ጌታ ፡ (አለ)
አለ ፡ ውዴ ፡ (አለ) ፡ አለ ፡ ጌታ ፡ (አለ ፡ አለ)