የመስቀል ፡ ፍቅርህ (Yemeskel Fekereh) - ጸሎት ፡ ስዩም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ጸሎት ፡ ስዩም
(Tselot Seyoum)

Tselot Seyoum 4.jpg


(4)

የመስቀል ፡ ፍቅርህ
(Yemeskel Fekereh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:54
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የጸሎት ፡ ስዩም ፡ አልበሞች
(Albums by Tselot Seyoum)

ስለ ፡ ሁኔታዎች ፡ ሳዝን ፡ ሲከፋኝ
የመስቀል ፡ ፍቅርህ ፡ ወዳጄ ፡ ትዝ ፡ እያለኝ
ሚደርስብኝ ፡ መከራ ፡ እንደ ፡ ብዙ ፡ ደስታ ፡ ቆጠርኩኝ
ውለታህ ፡ መዘነብኝ (፭x)

ግራ ፡ ሲገባኝ ፡ ጭልም ፡ ሲልብኝ
ወዲያው ፡ መልሶ ፡ ፍቅርህ ፡ ትውስ ፡ ሲለኝ
ነገሩን ፡ ትውት ፡ አድርጌው ፡ ጸልያለሁ/ዘምራለሁ
የታላቅነትህን ፡ ሚስጥር ፡ አስተውላለሁ
የታላቅነትህን ፡ ሚስጥር ፡ አስተውላለሁ (፪x)

ጌታን ፡ ለማስከበር ፡ ከፍሎ ፡ የለ ፡ ዋጋ
አንዱ ፡ በመጋዝ ፡ ሲሰነጠቅ ፡ ሌላው ፡ በጦር ፡ ሲወጋ
አንበሳ ፡ ሲበላ ፡ ሲጠበስ ፡ በዘይት
በድንጋይ ፡ ሲወገር ፡ ሲቃጠል ፡ በእሳት (፪x)

አያሳስበኝም ፡ መከራ ፡ ችግሩ
አያስጨንቀኝም ፡ ውርጭና ፡ ሀሩሩ
የጌታዬ ፡ ሥም ፡ ግን ፡ በዚም ፡ በዚያም ፡ መክበሩ
እሱ ፡ ነው ፡ ቁም ፡ ነገሩ (፬x)

አያሳስበኝም ፡ መከራ ፡ ችግሩ
አያስጨንቀኝም ፡ ውርጭና ፡ ሀሩሩ
የጌታዬ ፡ ሥም ፡ ግን ፡ በዚም ፡ በዚያም ፡ መክበሩ
እሱ ፡ ነው ፡ ቁም ፡ ነገሩ (፲፬x)