ለክብሩ ፡ ዘምሩ (Lekebru Zemeru) - ትዕግሥት ፡ ዓለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ትዕግሥት ፡ ዓለሙ
(Tigist Alemu)

Lyrics.jpg


(1)

ማራናታ
(Maranatha)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:17
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የትዕግሥት ፡ ዓለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Tigist Alemu)

አዝ፦ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ውዳሴና ፡ ዕልልታ
ይገባሃል ፡ አንተ ፡ የእኛ ፡ ጌታ
እግዚአብሔርን ፡ የምትወዱ ፡ ኦሆ ፡ የምትፈሩ ፡ አሃ
ተነሱ ፡ ለክብሩ ፡ ዘምሩ (፪x)

ሠማያዊ ፡ ሚስጢር ፡ የገለጸላችሁ
ከድቅድቅ ፡ ጨለማ ፡ መጥቶ ፡ ያወጣችሁ
ይህን ፡ እግዚአብሔርን ፡ እስኪ ፡ እናመስግነው
በዝማሬ ፡ ዕልልታ ፡ ክበር ፡ እንበለው

አዝ፦ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ውዳሴና ፡ ዕልልታ
ይገባሃል ፡ አንተ ፡ የእኛ ፡ ጌታ
እግዚአብሔርን ፡ የምትወዱ ፡ ኦሆ ፡ የምትፈሩ ፡ አሃ
ተነሱ ፡ ለክብሩ ፡ ዘምሩ (፪x)

የምድር ፡ ሁሉ ፡ ደስታ ፡ የፅዮን ፡ ተራራ
እግዚአብሔር ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ክብሩ ፡ የሚያስፈራ
እንደ ፡ እርሱ ፡ ያለ ፡ አምላክ ፡ ከቶ ፡ ስላላየን
ለታላቁ ፡ ጌታ ፡ እንሰግድለታለን

አዝ፦ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ውዳሴና ፡ ዕልልታ
ይገባሃል ፡ አንተ ፡ የእኛ ፡ ጌታ
እግዚአብሔርን ፡ የምትወዱ ፡ ኦሆ ፡ የምትፈሩ ፡ አሃ
ተነሱ ፡ ለክብሩ ፡ ዘምሩ (፪x)

አዲስን ፡ ዝማሬ ፡ ለእርሱ ፡ ዘምሩ
ታላቅነቱንም ፡ ግርማውንም ፡ አውሩ
ክብሩን ፡ ለአሕዛብ ፡ እንናገራለን
ተዓምራቱን ፡ ደግሞ ፡ እኛ ፡ እናወራለን

አዝ፦ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ውዳሴና ፡ ዕልልታ
ይገባሃል ፡ አንተ ፡ የእኛ ፡ ጌታ
እግዚአብሔርን ፡ የምትወዱ ፡ ኦሆ ፡ የምትፈሩ ፡ አሃ
ተነሱ ፡ ለክብሩ ፡ ዘምሩ (፪x)

የእርሱን ፡ በጐነት ፡ መልካምነቱን
ማለዳ ፡ ማለዳ ፡ ምሕረቱን ፡ ካየን
በፀጋው ፡ በፍቅሩ ፡ ጠብቆ ፡ ላቆመን
ቆመን ፡ ከነፍሳችን ፡ ምሥጋና ፡ እንሰጣለን

አዝ፦ ምሥጋናና ፡ ክብር ፡ ውዳሴና ፡ ዕልልታ
ይገባሃል ፡ አንተ ፡ የእኛ ፡ ጌታ
እግዚአብሔርን ፡ የምትወዱ ፡ ኦሆ ፡ የምትፈሩ ፡ አሃ
ተነሱ ፡ ለክብሩ ፡ ዘምሩ (፪x)

ተነሱ ፡ ለክብሩ ፡ ዘምሩ (፪x)