እኔም ፡ አምነዋለሁ (Eniem Amnewalehu) - ትዕግሥት ፡ ዓለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ትዕግሥት ፡ ዓለሙ
(Tigist Alemu)

Lyrics.jpg


(1)

ማራናታ
(Maranatha)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የትዕግሥት ፡ ዓለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Tigist Alemu)

የገባልኝን ፡ ቃል ፡ እስከሚፈፅመው
እግዚአብሔር ፡ ይተጋል
እኔም ፡ አምነዋለሁ (፬x)

የገባልኝን ፡ ቃል ፡ እስከሚፈፅመው
እግዚአብሔር ፡ ይተጋል
እኔም ፡ አምነዋለሁ (፬x)

ፍፁም ፡ የማይገባ ፡ የማይመስል ፡ ነገር
እንደምን ፡ ይሆናል ፡ የተባለ ፡ ቢሆን
የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ በቃሉ ፡ የታመነ
እውን ፡ ያደርገዋል ፡ ተስፋ ፡ ከእርሱ ፡ ካለ

ስለዚህ ፡ አምላኬን ፡ እጠብቃለሁኝ
እርሱ ፡ ያየልኝን ፡ እኔም ፡ እስካየው (፪x)

ቀናቶች ፡ ቢረዝሙ ፡ ችግሩም ፡ ቢበዛ
እምነቴም ፡ ቢፈተን ፡ ጠላትም ፡ ቢነሳ
ቃል ፡ ተናግሯልና ፡ ይሆናል ፡ አይቀርም
ጌታዬ ፡ ሲከፍተው ፡ ማንም ፡ አይዘጋውም

ስለዚህ ፡ አምላኬን ፡ እጠብቃለሁኝ
እርሱ ፡ ያየልኝን ፡ እኔም ፡ እስካየው (፪x)

ዓይኖቹ ፡ ያዩኛል ፡ ጆሮውም ፡ ይሰማኛል
የልቤን ፡ ጥያቄ ፡ ጌታዬ ፡ ያውቀዋል
መልስ ፡ እስከሚመጣ ፡ እስከሚጐበኘኝ
አፅንቶ ፡ የሚያቆም ፡ የተስፋ ፡ ቃል ፡ አለኝ

ስለዚህ ፡ አምላኬን ፡ እጠብቃለሁኝ
እርሱ ፡ ያየልኝን ፡ እኔም ፡ እስካየው (፪x)