ባለፀጋ (Baletsega) - ትዕግሥት ፡ ዓለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ትዕግሥት ፡ ዓለሙ
(Tigist Alemu)

Lyrics.jpg


(1)

ማራናታ
(Maranatha)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 4:19
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የትዕግሥት ፡ ዓለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Tigist Alemu)

አዝ፦ በምሕረቱ ፡ ባለፀጋ ፡ ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከክርስቶስ ፡ ጋራ ፡ ሕይወት ፡ ሰጠኝ
እንዲሁ ፡ በፀጋው ፡ አፀደቀኝ (፪x)

ምንድነው ፡ ያቆመኝ ፡ ከፃድቃኖች ፡ ስፍራ
ስለ ፡ ምህረትህ ፡ ልናገር ፡ ላወራ
ለካስ ፡ ከማህፀን ፡ ጌታዬ ፡ አስቦኛል
ያን ፡ ሁሉ ፡ ኀጢአቴን ፡ በደሙ ፡ አጥቦልኛል

አዝ፦ በምሕረቱ ፡ ባለፀጋ ፡ ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከክርስቶስ ፡ ጋራ ፡ ሕይወት ፡ ሰጠኝ
እንዲሁ ፡ በፀጋው ፡ አፀደቀኝ (፪x)

እንዴት ፡ አደረገኝ ፡ እኔን ፡ አዲስ ፡ ፍጥረት
በመንፈሱ ፡ ገዛኝ ፡ ጌታዬ ፡ በእርሱ ፡ እምነት
ማለዳ ፡ ስነሳ ፡ ፍቅሩ ፡ ትዝ ፡ ይለኛል
አዲስ ፡ ሰው ፡ መሆኔ ፡ ሁሌም ፡ ይደንቀኛል

አዝ፦ በምሕረቱ ፡ ባለፀጋ ፡ ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከክርስቶስ ፡ ጋራ ፡ ሕይወት ፡ ሰጠኝ
እንዲሁ ፡ በፀጋው ፡ አፀደቀኝ (፪x)

ፀጋው ፡ በእምነት ፡ እኔን ፡ አድኖኛል
የእግዚአብሔር ፡ ስጦታ ፡ በእርግጥ ፡ በዝቶልኛል
ታዲያ ፡ ምን ፡ አለና ፡ ከእኔ ፡ የምለው ፡ ሥራ
ታላቅነትህን ፡ ደፍሬ ፡ ላወራ

አዝ፦ በምሕረቱ ፡ ባለፀጋ ፡ ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከክርስቶስ ፡ ጋራ ፡ ሕይወት ፡ ሰጠኝ
እንዲሁ ፡ በፀጋው ፡ አፀደቀኝ (፪x)

እንደ ፡ ኀጢአቴ ፡ ብዛት ፡ ጌታዬ ፡ አላረገብኝ
እንደ ፡ በደሌም ፡ ከቶ ፡ አልከፈለኝ
ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ስማ ፡ እግዚአብሔር ፡ ወዶኛል
ምሕረት ፡ ቸርነቱ ፡ ፀጋው ፡ በዝቶልኛል

አዝ፦ በምሕረቱ ፡ ባለፀጋ ፡ ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከወደደኝ ፡ ፍቅሩ ፡ የተነሳ
ከክርስቶስ ፡ ጋራ ፡ ሕይወት ፡ ሰጠኝ
እንዲሁ ፡ በፀጋው ፡ አፀደቀኝ (፪x)

ፍቅሩ ፡ በዝቶልኛል
ምህረት በዝቶልኛል
ፀጋው ፡ በዝቶልኛል
ሰላም ፡ በዝቶልኛል (፪x)