በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ (Bekerestos Eyesus) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(5)

የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ
(Yenazretu Eyesus)

ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:01
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የእግዚአብሔር ፡ ፈቃድ ፡ ለልጆቹ
ይህ ፡ ነው ፡ መንገዱ ፡ ለምርጦቹ
ብድራታቸውን ፡ ያስተዋሉ
የጌታን ፡ መስቀል ፡ ይመርጣሉ

አዝ፦ በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ እግዚአብሔርን
እየመሰሉ ፡ ሊኖሩ ፡ የሚወዱ ፡ ሁሉ
ስለ ፡ ሥሙ ፡ ይሰደዳሉ
እንደ ፡ ወርቅም ፡ ይፈተናሉ
በመጨረሻም ፡ ሁሉንም ፡ አልፈው
የዘለዓለምን ፡ ሕይወት ፡ ይወርሳሉ

ለዚች ፡ ዓለም ፡ የሚመቹ
ነውረኛውን ፡ ትርፍ ፡ ያከማቹ
በኩርነታቸውን ፡ አቃለዋል
በሥጋ ፡ ምቾት ፡ ተጠምደዋል

አዝ፦ በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ እግዚአብሔርን
እየመሰሉ ፡ ሊኖሩ ፡ የሚወዱ ፡ ሁሉ
ስለ ፡ ሥሙ ፡ ይሰደዳሉ
እንደ ፡ ወርቅም ፡ ይፈተናሉ
በመጨረሻም ፡ ሁሉንም ፡ አልፈው
የዘለዓለምን ፡ ሕይወት ፡ ይወርሳሉ

ጌታን ፡ አክብሮ ፡ መጐስቆሉ
እንደ ፡ ጉድፍ ፡ የትም ፡ መጣሉ
የመዳን ፡ ምልክት ፡ ክብራችን
ድል ፡ መምቻችን ፡ ነው ፡ መስቀላችን

አዝ፦ በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ እግዚአብሔርን
እየመሰሉ ፡ ሊኖሩ ፡ የሚወዱ ፡ ሁሉ
ስለ ፡ ሥሙ ፡ ይሰደዳሉ
እንደ ፡ ወርቅም ፡ ይፈተናሉ
በመጨረሻም ፡ ሁሉንም ፡ አልፈው
የዘለዓለምን ፡ ሕይወት ፡ ይወርሳሉ

ጌታን ፡ ምሰሉ ፡ በኑሮአችሁ
ከጠፊ ፡ ዓለም ፡ ምን ፡ አላችሁ
ውጡ ፡ ተለዩ ፡ እባካችሁ
ፍፁማን ፡ ሁኑ ፡ በልባችሁ

አዝ፦ በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ እግዚአብሔርን
እየመሰሉ ፡ ሊኖሩ ፡ የሚወዱ ፡ ሁሉ
ስለ ፡ ሥሙ ፡ ይሰደዳሉ
እንደ ፡ ወርቅም ፡ ይፈተናሉ
በመጨረሻም ፡ ሁሉንም ፡ አልፈው
የዘለዓለምን ፡ ሕይወት ፡ ይወርሳሉ