አንተ ፡ የምትተኛ (Ante Yemetetegna) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(5)

የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ
(Yenazretu Eyesus)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 3:39
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የሰማይ ፡ ብርሃን ፡ ጨለማውን ፡ ገፍፎ
ሲዖል ፡ ድል ፡ ተነስቶ ፡ ሞትም ፡ ተሸንፎ
በኃጢያት ፡ ተወግተው ፡ ደክመው ፡ ለወደቁ
ጥሪው ፡ ያስተጋባል ፡ ሙታን ፡ እንዲነቁ

አዝ፦ አንተ ፡ የምትተኛ ፡ ኢየሱስ ፡ ይጠራሃል
በሰማዩ ፡ ፍቅር ፡ ይቀሰቅስሃል
ከተሸሸግበት ፡ ከሙታን ፡ መቃብር ፡ ተነሳ ፡ ይልሃል

ማየት ፡ በሌለበት ፡ መስማት ፡ በጠፋበት
ምሬትና ፡ ፀፀት ፡ ለቅሶ ፡ ከሞላበት
ምንድን ፡ ነው ፡ የጣለህ ፡ እንደምንስ ፡ መጣህ
ከሕያዋን ፡ ምድር ፡ ፈጥነህ ፡ ለምን ፡ ወጣህ

አዝ፦ አንተ ፡ የምትተኛ ፡ ኢየሱስ ፡ ይጠራሃል
በሰማዩ ፡ ፍቅር ፡ ይቀሰቅስሃል
ከተሸሸግበት ፡ ከሙታን ፡ መቃብር ፡ ተነሳ ፡ ይልሃል

ከእንቅልፍ ፡ የምትነሳበት ፡ ሰዓት ፡ ነው
ጊዜህን ፡ መርምረው ፡ ዘመኑን ፡ እወቀው
እንግዲያውስ ፡ ንቃ ፡ ተነስ ፡ ተመላለስ
አንተም ፡ ተመልሰህ ፡ የጠፉትን ፡ መልስ

አዝ፦ አንተ ፡ የምትተኛ ፡ ኢየሱስ ፡ ይጠራሃል
በሰማዩ ፡ ፍቅር ፡ ይቀሰቅስሃል
ከተሸሸግበት ፡ ከሙታን ፡ መቃብር ፡ ተነሳ ፡ ይልሃል

ድፍረትህን ፡ አትጣል ፡ ብድራት ፡ አለና
በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ኃይል ፡ ተነስ ፡ እንደገና
የደከመው ፡ እጅህ ፡ የዛለው ፡ ጉልበትህ
ዳግም ፡ ተጠናክሮ ፡ ያፈራል ፡ ሕይወትህ

አዝ፦ አንተ ፡ የምትተኛ ፡ ኢየሱስ ፡ ይጠራሃል
በሰማዩ ፡ ፍቅር ፡ ይቀሰቅስሃል
ከተሸሸግበት ፡ ከሙታን ፡ መቃብር ፡ ተነሳ ፡ ይልሃል