ቃሉን ፡ ከቶ ፡ የማያጥፍ (Qalun Keto Yemayatef) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(7)

ያይሃል
(Yayehal)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 4:17
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ ቃሉን ፡ ከቶ ፡ የማያጥፍ
ታማኝ ፡ አምላክ ፡ ነውና
የነገረንን ፡ ሁሉ ፡ ፈጽሞት ፡ አይተናልና
ከፍ ፡ ከፍ ፡ እናደርገዋለን ፡ በምሥጋና

የኃጢአትን ፡ ከተማ ፣ የዲያብሎስን ፡ ሥራ
ሲያፈራርሰው ፡ አይተናል ፡ ያን ፡ ምሽግ ፡ ያንን ፡ ተራራ
ጌታችን ፡ ኢየሱስ ፡ ተገልጦ ፣ የሕይወታችን ፡ ብርሃን
የተስፋ ፡ ቃሉን ፡ ፈጸመው ፡ በሞቱ ፡ እኛን ፡ በማዳን

አዝ፦ ቃሉን ፡ ከቶ ፡ የማያጥፍ
ታማኝ ፡ አምላክ ፡ ነውና
የነገረንን ፡ ሁሉ ፡ ፈጽሞት ፡ አይተናልና
ከፍ ፡ ከፍ ፡ እናደርገዋለን ፡ በምሥጋና

በሰላምና ፡ በሕይወት ፣ በበጐ ፡ ነገርም ፡ ምክር
አበሳችን ፡ እንዲወገድ ፣ እሮሮአችንም ፡ እንዲቀር
በእኛ ፡ ያለውን ፡ ነገር ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር ፡ አይቶ
ቀንበራችንን ፡ ሰበረው ፡ ለቅሶአችንን ፡ እርሱ ፡ ሰምቶ

አዝ፦ ቃሉን ፡ ከቶ ፡ የማያጥፍ
ታማኝ ፡ አምላክ ፡ ነውና
የነገረንን ፡ ሁሉ ፡ ፈጽሞት ፡ አይተናልና
ከፍ ፡ ከፍ ፡ እናደርገዋለን ፡ በምሥጋና

የሲኦልን ፡ ማስፈራራት ፣ የመከራን ፡ አውሎ ፡ ነፋስ
የኃያላኑን ፡ ጭካኔ ፣ የቁጣቸውን ፡ እስትንፋስ
የማዕበሉን ፡ ሁሉ ፡ ጩኸት ፣ የዓመጽንም ፡ ዝማሬ
በሥልጣኑ ፡ ቃል ፡ ገስጾ ፡ ዝም ፡ አሰኝቶታል ፡ ዛሬ

አዝ፦ ቃሉን ፡ ከቶ ፡ የማያጥፍ
ታማኝ ፡ አምላክ ፡ ነውና
የነገረንን ፡ ሁሉ ፡ ፈጽሞት ፡ አይተናልና
ከፍ ፡ ከፍ ፡ እናደርገዋለን ፡ በምሥጋና

የመማጸኛ ፡ ግንብ ፡ ነው ፣ የድሆች ፡ ሁሉ ፡ መጠጊያ
ምቹ ፡ መሸሸጊያ ፡ ዓለት ፡ የለንም ፡ ከኢየሱስ ፡ ወዲያ
ብዙዎቹም ፡ ይድናሉ ፡ ገብተው ፡ ከዚህ ፡ መጠለያ
ስለሚሆንልን ፡ ሁሉ ፡ ይክበር ፡ ጌታ ፣ ሃሌሉያ!

አዝ፦ ቃሉን ፡ ከቶ ፡ የማያጥፍ
ታማኝ ፡ አምላክ ፡ ነውና
የነገረንን ፡ ሁሉ ፡ ፈጽሞት ፡ አይተናልና
ከፍ ፡ ከፍ ፡ እናደርገዋለን ፡ በምሥጋና