የፍጥረት ፡ ገዢ ፡ ተቆጣጣሪ (Yefetret Gejzi Tekotatari) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(2)

እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው
(Egziabhier Menfes New)

ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 3:10
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በሰልፉ ፡ ሜዳ ፡ በዝቶ ፡ ጠላቴ
ፍርሃት ፡ ሲያርደኝ ፡ ፈርቶ ፡ ጉልበቴ
ጠፍሁ ፡ ብዬ ፡ ስል ፡ ወየው ፡ ጌታዬ
ከፊቴ ፡ ያልፋል ፡ ኢየሱስ ፡ ጋሻዬ

አዝ፦ ካፈጠጠብኝ ፡ በዓለም ፡ ካለዉ
እጅግ ፡ ይበልጣል ፡ በእኔ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ገዢ ፡ ተቆጣጣሪው
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው

ጠላት ፡ እንደ ፡ ንብ ፡ ከቦኝ ፡ ቢመጣ
ምሽጌን ፡ ትቼ ፡ እኔም ፡ አልወጣም
በእግዚአብሔር ፡ ሥም ፡ እሸንፋለሁ
ጐልያድም ፡ ወድቆ ፡ በዓይኔ ፡ አየዋለሁ

አዝ፦ ካፈጠጠብኝ ፡ በዓለም ፡ ካለዉ
እጅግ ፡ ይበልጣል ፡ በእኔ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ገዢ ፡ ተቆጣጣሪው
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው

ፅኑ ፡ ኃያሉ ፡ የአምላክ ፡ ጦረኛ
አንዱ ፡ ለሺህ ፡ ነው ፡ የእምነት ፡ አርበኛ
ከአመፀኞች ፡ እጅ ፡ ደሙን ፡ በትኖ
ፍሬውን ፡ ያበዛል ፡ በአምላኩ ፡ ታምኖ

አዝ፦ ካፈጠጠብኝ ፡ በዓለም ፡ ካለዉ
እጅግ ፡ ይበልጣል ፡ በእኔ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ገዢ ፡ ተቆጣጣሪው
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው

ረዳት ፡ እንዳለኝ ፡ ጠላቴም ፡ ያያል
እንደ ፡ ዘበተ ፡ መቼ ፡ ይቀራል
የመስቀል ፡ ፅዋ ፡ እኔም ፡ ጠጣለሁ
ድል ፡ ይታወጃል ፡ አሻገራለሁ

አዝ፦ ካፈጠጠብኝ ፡ በዓለም ፡ ካለዉ
እጅግ ፡ ይበልጣል ፡ በእኔ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ገዢ ፡ ተቆጣጣሪው
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው (፪x)