ተጠፍሬ፡ ያየኝ (Teteferie Yayehegn) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(2)

እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው
(Egziabhier Menfes New)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:05
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በጉልበቴ ፡ ያለሁ ፡ ገና ፡ ያልተነካሁኝ
በመንገድ ፡ አጠገብ ፡ በውጭ ፡ የታሰርኩኝ
ነጻነት ፡ የሌለኝ ፡ ውርንጫ ፡ ነበርኩኝ
ሳላውቅህ ፡ አውቀኸኝ ፡ አንተ ፡ ግን ፡ ፈታኸኝ

አዝ፦ ተጠፍሬ ፡ ያየኝ ፡ ያለ ፡ ውዴታዬ
ነጻነት ፡ የሰጠኝ ፡ ወዳጅ ፡ አለኝታዬ
ማነው ፡ ከአንተ ፡ በቀር ፡ ባለ ፡ ውለታዬ
ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ ፡ ተመሥገን ፡ ጌታዬ (፪x)

በዚህ ፡ በጉልበቴ ፡ ለአንተ ፡ ክብር ፡ ሮጬ
እባብና ፡ ጊንጡን ፡ በሥምህ ፡ ረግጬ
መሸለሜን ፡ ሰምቶ ፡ ጠላት ፡ አኮረፈ
አንተን ፡ በላዬ ፡ ሲያይ ፡ ጥላው ፡ ተገፈፈ

አዝ፦ ተጠፍሬ ፡ ያየኝ ፡ ያለ ፡ ውዴታዬ
ነጻነት ፡ የሰጠኝ ፡ ወዳጅ ፡ አለኝታዬ
ማነው ፡ ከአንተ ፡ በቀር ፡ ባለ ፡ ውለታዬ
ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ ፡ ተመሥገን ፡ ጌታዬ (፪x)

ከእሥራት ፡ ፈተኸኝ ፡ በእኔ ፡ ልትቀመጥ
ይህን ፡ ታላቅ ፡ ዕድል ፡ ለምስኪኑ ፡ ልትሰጥ
ለመሆኑ ፡ እኔ ፡ ኧረ ፡ እኔ ፡ ማን ፡ ነኝ
ይገባኛል ፡ እንዴ ፡ ለዚህ ፡ ልትመርጠኝ

አዝ፦ ተጠፍሬ ፡ ያየኝ ፡ ያለ ፡ ውዴታዬ
ነጻነት ፡ የሰጠኝ ፡ ወዳጅ ፡ አለኝታዬ
ማነው ፡ ከአንተ ፡ በቀር ፡ ባለ ፡ ውለታዬ
ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ ፡ ተመሥገን ፡ ጌታዬ (፪x)

ሆሴና ፡ በአርያም ፡ እያሉ ፡ ቢጮሁ
ልብሳቸውንና ፡ ቅጠል ፡ ቢያነጥፉ
የነገር ፡ ጀማሪ ፡ አንተ ፡ በላዬ ፡ ነህ
ክብሩ ፡ የራስህ ፡ ነው ፡ ኑር ፡ ዘለዓለም ፡ ከብረህ
ውርጭላው ፡ ተፈትቶ ፡ የክበር ፡ ዕቃ ፡ ሆኗል
ነጻነትን ፡ ሰጥቶት ፡ ጌታው ፡ ከብሮበታል
የተፈታውን ፡ ሳይሆን ፡ የፈታውን ፡ አክብሩ
ሆሳዕና ፡ በሉ ፡ መንገሡንም ፡ አውሩ (፪x)