እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው (Egziabhier Menfes New) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(2)

እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው
(Egziabhier Menfes New)

ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:38
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው ፡ በሥጋም ፡ አይደፈር
እጅግም ፡ ታላቅ ፡ ነው ፡ በሰው ፡ የማይገመት
ዛሬም ፡ እንደቀድሞው ፡ ክንዱ ፡ ኃያል ፡ ያደርጋል
ቢወዱም ፡ ቢጠሉም ፡ ኢየሱስ ፡ ይነግሣል

አዝ፦ በሰማይ ፡ በምድርም ፡ ሙሉ ፡ ስልጣን ፡ ያለው
የሚለውጥህ ፡ እንጂ ፡ የማይለውጠው
አልፋ ፡ ኦሜጋ ፡ ማለት ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

ሥሙን ፡ በመታመን ፡ ሲቀርቡት ፡ ይቀርባል
በደከመች ፡ ሕይወት ፡ ብርታት ፡ ይጨምራል
ሞገዱን ፡ ፀጥ ፡ አድርጐ ፡ ሰላምን ፡ ይሰጣል
ምንጩን ፡ አጠጥቶ ፡ በረሃን ፡ ያለማል

አዝ፦ በሰማይ ፡ በምድርም ፡ ሙሉ ፡ ስልጣን ፡ ያለው
የሚለውጥህ ፡ እንጂ ፡ የማይለውጠው
አልፋ ፡ ኦሜጋ ፡ ማለት ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

የማይታየው ፡ ባህሪ ፡ የዘላለም ፡ ኃይሉ
በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ኃይል ፡ በእውነት ፡ ሲያስተውሉ
ከጥንትም ፡ ጀምሮ ፡ ከተሰሩት ፡ ደምቆ
ይኖራል ፡ ኢየሱስ ፡ ህልውናው ፡ ታውቆ

አዝ፦ በሰማይ ፡ በምድርም ፡ ሙሉ ፡ ስልጣን ፡ ያለው
የሚለውጥህ ፡ እንጂ ፡ የማይለውጠው
አልፋ ፡ ኦሜጋ ፡ ማለት ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

የተዓምራት ፡ አምላክ ፡ ክንዱ ፡ መች ፡ አጠረ
ሰው ፡ ያወቀ ፡ መስሎት ፡ ብዙ ፡ የመረመረ
ኃጢአትን ፡ አጣጥሞ ፡ ለፍርድ ፡ እየኖረ
ጌታን ፡ የለም ፡ ብሎ ፡ እጁን ፡ አጣመረ

አዝ፦ በሰማይ ፡ በምድርም ፡ ሙሉ ፡ ስልጣን ፡ ያለው
የሚለውጥህ ፡ እንጂ ፡ የማይለውጠው
አልፋ ፡ ኦሜጋ ፡ ማለት ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው