ምሥጋና ፡ የሚገባውን (Mesgana Yemigebawen) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(1)

እግዚአብሔር ፡ ኃያል
(Egziabhier Hayal)

ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:11
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

የአመጽ ፡ ፈሳሽ ፡ ሲያስፈራራኝ ፡ የሲዖል ፡ ጣርም ፡ ሲከበኝ
አምላክህ ፡ የታለ ፡ ሲለኝ ፡ ባላንጣዬ ፡ ሲያፌዝብኝ
ከመሠረቴ ፡ ሊነቅለኝ ፡ ቆይ ፡ ብቻ ፡ ሲል ፡ ሲዝትብኝ
የጌታን ፡ ሥም ፡ እጠራለሁ ፡ ከጠላቴም ፡ እድናለሁ

አዝ፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

የጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ለእኔ ፡ የፀና ፡ ግንብ ፡ ነውና
እስከዛሬም ፡ እርሱን ፡ ጠርቶ ፡ ማንም ፡ አላፈረምና
በኪሩቤል ፡ የሚኖረው ፡ ሙሉ ፡ ተስፋ ፡ ስለሰጠኝ
ታምኜ ፡ ሥሙን ፡ እጠራለሁ ፡ ከጠላቴም ፡ እድናለሁ

አዝ፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

በጨነቀኝ ፡ ጊዜ ፡ ሁሉ ፡ እግዚአብሔርን ፡ ጠራሁት
ስቅስቅ ፡ እያልኩኝ ፡ በእንባ ፡ የሆዴን ፡ ብሶት ፡ ነገርኩት
ከዚያም ፡ በበቀል ፡ ወረደ ፡ ከሰማይ ፡ አንጐደጐደ
በመብረቁ ፡ አወካቸው ፡ በፍላጻው ፡ በተናቸው

አዝ፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)

ለጥርሶቻቸው ፡ ንክሻ ፡ አላደረገኝምና
ከተዘረጋብኝ ፡ ወጥመድ ፡ ሁሌ ፡ አድኖኛልና
አርነቴን ፡ ከሚቀማ ፡ ከሰይጣን ፡ ጋርዶኛልና
ሥሙ ፡ ይክበር ፡ ሃሌሉያ ፡ እያልኩኝ ፡ ልኑር ፡ በእርሱ ፡ ጉያ

አዝ፦ ምሥጋና ፡ የሚገባውን
እግዚአብሔርን ፡ እጠራለሁ
ከጠላቶቼም ፡ እድናለሁ (፪x)