ልጅነቴ ፡ አላለቀም (Lejenetie Alaleqem) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(1)

እግዚአብሔር ፡ ኃያል
(Egziabhier Hayal)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 2:35
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ ልጅነቴ ፡ አላለቀም ፡ ነኝና ፡ ብላቴና
ሙሉ ፡ ሰው ፡ አድርገኝ ፡ ጌታ ፡ ቃልህን ፡ አብላኝና (፪x)

በግብዝነት ፡ ተሯሩጬም ፡ ከእውነትህም ፡ ተሳሰቼ
በስሜት ፡ ተገፋፍቼ ፡ የቃልህን ፡ ሙላት ፡ አጥቼ
እንዳልጠፋ ፡ በጠላት ፡ ተጠቅቼ

አዝ፦ ልጅነቴ ፡ አላለቀም ፡ ነኝና ፡ ብላቴና
ሙሉ ፡ ሰው ፡ አድርገኝ ፡ ጌታ ፡ ቃልህን ፡ አብላኝና (፪x)

ለጋነቴ ፡ እኔን ፡ አጋልጦኝ ፡ መከራውም ፡ አጠውልጐኝ
አውሎ ፡ ነፋስ ፡ አፍገምግሞኝ ፡ የአሸዋው ፡ መሠረት ፡ አዝሞኝ
ክፉኛ ፡ ገፍትሮ ፡ እንዳይጥለኝ

አዝ፦ ልጅነቴ ፡ አላለቀም ፡ ነኝና ፡ ብላቴና
ሙሉ ፡ ሰው ፡ አድርገኝ ፡ ጌታ ፡ ቃልህን ፡ አብላኝና (፪x)

ወተት ፡ ብቻ ፡ መጋቱን ፡ ትቼ ፡ አጥንቱንም ፡ ደግሞ ፡ በልቼ
እንደ ፡ ህጻን ፡ ማሰቤ ፡ ቀርቶ ፡ በጐልማሳነት ፡ ተተክቶ
ላይ ፡ እሻለሁ ፡ ሕይወቴ ፡ ተገንብቶ

አዝ፦ ልጅነቴ ፡ አላለቀም ፡ ነኝና ፡ ብላቴና
ሙሉ ፡ ሰው ፡ አድርገኝ ፡ ጌታ ፡ ቃልህን ፡ አብላኝና (፪x)