From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት ።
|
አንድን ፡ ነገር ፡ ሽቼ ፡ ደጅ ፡ ጠናለሁኝ
ፈቃድህ ፡ ከሆነ ፡ በዓይንህ ፡ ተመልከተኝ
ያቺን ፡ ብሩክ ፡ እጅህን ፡ ዘርጋብኝ
አዝ፦ እንባዬን ፡ አይተህ ፡ ጌታ
ለቅሶዬን ፡ ሰምተህ ፡ ጌታ
መሻቴን ፡ ስጠኝና ፡ ኢየሱስ ፡ ላመስግንህ (፪x)
አንተን ፡ ተስፋ ፡ አድርጌ ፡ በቃልህ ፡ ፀንቼ
መልሴን ፡ አጠብቃለሁ ፡ በተመስጦ ፡ ሆኜ
ታማኝነትህን ፡ ተማምኜ
አዝ፦ እንባዬን ፡ አይተህ ፡ ጌታ
ለቅሶዬን ፡ ሰምተህ ፡ ጌታ
መሻቴን ፡ ስጠኝና ፡ ኢየሱስ ፡ ላመስግንህ (፪x)
በጐ ፡ ስጦታና ፡ ፍፁም ፡ በረከት ፡ ሁሉ
ከብርሃናት ፡ አባት ፡ ከላይ ፡ ይወርዳሉ
ከዙፋንህ ፡ ይንቆረቆራሉ
አዝ፦ እንባዬን ፡ አይተህ ፡ ጌታ
ለቅሶዬን ፡ ሰምተህ ፡ ጌታ
መሻቴን ፡ ስጠኝና ፡ ኢየሱስ ፡ ላመስግንህ (፪x)
መራራነቴ ፡ ያብቃ ፡ እሾህነቴም ፡ ያብቃ
መፈራረሴም ፡ ያብቃ ፡ በአንተ ፡ ፀጋ ፡ ልገንባ
ጐስቋላነቴን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እንካ
አዝ፦ እንባዬን ፡ አይተህ ፡ ጌታ
ለቅሶዬን ፡ ሰምተህ ፡ ጌታ
መሻቴን ፡ ስጠኝና ፡ ኢየሱስ ፡ ላመስግንህ (፪x)
|