Tesfaye Gabisso/Christian Teshagere/Zemenu Fetene

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ ዘመኑ ፈጠነ አልበም ክርስቲያን ተሻገረ

አዝ ዘመኑ ፈጠነ ሮጠ ገሰገሰ የጌታችን መምጫ ጊዜያቱ ደረሰ ሰዎች ቶሎ በሉ መከሩን ሰብስቡ የተጣለብንን አደራ አስቡ

ሰዓቱ ሊሞላ በቅርብ ነው ያለው መለከት ሊነፋ በቅርብ ነው ያለው ነገሩ ሊያከትም በቅርብ ነው ያለው ጌታም ከተፍ ሊል በቅርብ ነው ያለው

አዝ ዘመኑ ፈጠነ ሮጠ ገሰገሰ የጌታችን መምጫ ጊዜያቱ ደረሰ ሰዎች ቶሎ በሉ መከሩን ሰብስቡ የተጣለብንን አደራ አስቡ

ሰማያት ሲከብዱ ደመናው ሲጠቁር ምድራችን ስታምር ነገር ሲቀያየር ምን አዚም ኖረብን እንዳናይ ጊዜ አጥሮን ተው ነቃ እንበል እናቁም አንቅልፍን

አዝ ዘመኑ ፈጠነ ሮጠ ገሰገሰ የጌታችን መምጫ ጊዜያቱ ደረሰ ሰዎች ቶሎ በሉ መከሩን ሰብስቡ የተጣለብንን አደራ አስቡ

ሰዉ ሲተራመስ ሞትን ለመሳለም ከአምላክ ተለይቶ በኃጢያት ሲታመን ጠቢቡ እንኳን ሲስት በሰይጣን ሲታለል ተነሱ አንናገር ለነፍስ እንታገል

አዝ ዘመኑ ፈጠነ ሮጠ ገሰገሰ የጌታችን መምጫ ጊዜያቱ ደረሰ ሰዎች ቶሎ በሉ መከሩን ሰብስቡ የተጣለብንን አደራ አስቡ

ለራሱ ያልሞተ እራሱን ያልከዳ ጌታ የማይገዛው ለኃጥያት ያልታገለ በምኑ ይመስክር ልቡ ይንቀጠቀጣል ዋጋም ክፈል ሲባል ትቶ ይፈረጥጣል

አዝ ዘመኑ ፈጠነ ሮጠ ገሰገሰ የጌታችን መምጫ ጊዜያቱ ደረሰ ሰዎች ቶሎ በሉ መከሩን ሰብስቡ የተጣለብንን አደራ አስቡ