ኢየሱስን ፡ ለብሰህ (Eyesusen Lebseh) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(3)

ክርስቲያን ፡ ተሻገረ
(Christian Teshagere)

ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 3:34
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የሚቀጠቅጥ ፡ በአንተ ፡ ላይ ፡ ወጥቷል ፡ በጠላት ፡ ተከበሃል
ክርስቲያን ፡ ተጠንቀቅ ፡ ዙሪያህን ፡ አስተውል
ጉልበትህ ፡ አይላላ ፡ ጠንክረህ ፡ ተዋጋ
ብድራትን ፡ አይተህ ፡ ያለልህን ፡ ዋጋ

አዝ፦ ኢየሱስን ፡ ለብሰህ
የጦር ፡ ዕቃህን ፡ አንስተህ
በእርሱ ፡ መልካም ፡ ጦርነት ፡ ተዋጋ
ኢየሱስ ፡ ያሸንፋል ፡ ለድሉ ፡ አትስጋ

በጦርነት ፡ ላይ ፡ መቁሰልም ፡ አለ ፡ ሞትም ፡ ቢሆን ፡ ጥቅም ፡ ነው
ለጨለማው ፡ ገዢ ፡ እጅህን ፡ አትስጠው
እስከ ፡ ሞትም ፡ ታመን ፡ ነፍስህን ፡ አታክብራት
ለታመነው ፡ ፈጣሪ ፡ አሳልፈህ ፡ ስጣት

አዝ፦ ኢየሱስን ፡ ለብሰህ
የጦር ፡ ዕቃህን ፡ አንስተህ
በእርሱ ፡ መልካም ፡ ጦርነት ፡ ተዋጋ
ኢየሱስ ፡ ያሸንፋል ፡ ለድሉ ፡ አትስጋ

ባለጋራህ ፡ ዲያብሎስ ፡ ሊውጥህ ፡ እያገሳብህ ፡ ነውና
ከድምፁ ፡ አትፍራ ፡ አባትህ ፡ አለና
መንጋጋውን ፡ ዘግቶ ፡ ከአፉ ፡ ያስጥልሃል
ከቶም ፡ እንደማይጥልህ ፡ በግልጽ ፡ ያሳየዋል

አዝ፦ ኢየሱስን ፡ ለብሰህ
የጦር ፡ ዕቃህን ፡ አንስተህ
በእርሱ ፡ መልካም ፡ ጦርነት ፡ ተዋጋ
ኢየሱስ ፡ ያሸንፋል ፡ ለድሉ ፡ አትስጋ

የውጊያው ፡ ጊዜ ፡ አሁን ፡ ነው ፡ ወንድም
ተነስ ፡ ተጋጠመው ፡ ድል ፡ ትነሳዋለህ
በርትተህ ፡ ታገለው ፡ የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ ጋሻ ፡ ይሆንሃል
ለአገርህም ፡ አብቅቶ ፡ አክሊል ፡ ይሰጥሃል

አዝ፦ ኢየሱስን ፡ ለብሰህ
የጦር ፡ ዕቃህን ፡ አንስተህ
በእርሱ ፡ መልካም ፡ ጦርነት ፡ ተዋጋ
ኢየሱስ ፡ ያሸንፋል ፡ ለድሉ ፡ አትስጋ