ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ (Basqemetkegn Bota) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(3)

ክርስቲያን ፡ ተሻገረ
(Christian Teshagere)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 3:53
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

ገነት ፡ መኖሪያዬን ፡ ሰርተህ ፡ ውብ ፡ አድርገህ
ምግቤን ፡ ያለ ፡ ድካም ፡ እንድበላ ፡ ብለህ
ያስቀመጥክኝን ፡ ሰው ፡ ወሬ ፡ ሲደልለኝ
እጦት ፡ ሲያራቁተኝ ፡ በቸልታ ፡ አትየኝ

አዝ፦ ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ ፡ ፀንቼ ፡ እንድቆይ
መጥተህ ፡ ስትጐበኘኝ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ እንዲልህ
ፀጋህን ፡ አብዛልኝ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እባክህ

ልቤ ፡ እየቸኮለ ፡ እግሬ ፡ ሮጥ ፡ እያለ
ውርደትን ፡ ለማየት ፡ ዓይኔ ፡ እየከጀለ
ድንበር ፡ እየጣሰ ፡ ከኃጢአት ፡ እየዋለ
የማታ ፡ የማታም ፡ ሚዛኔ ፡ ቀለለ

አዝ፦ ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ ፡ ፀንቼ ፡ እንድቆይ
መጥተህ ፡ ስትጐበኘኝ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ እንዲልህ
ፀጋህን ፡ አብዛልኝ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እባክህ

የጭንጫ ፡ ቡቃያ ፡ ፈጥኖ ፡ የበቀለ
ፀሐይ ፡ ስትወጣ ፡ ነዶ ፡ ተቃጠለ
አንተን ፡ ሆኜ : እኔ ፡ ፍሬን ፡ እንዳፈራ
አንስተህ ፡ አትጣለኝ ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ አደራ

አዝ፦ ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ ፡ ፀንቼ ፡ እንድቆይ
መጥተህ ፡ ስትጐበኘኝ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ እንዲልህ
ፀጋህን ፡ አብዛልኝ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እባክህ

ቸኮል ፡ ያለ ፡ ሳዖል ፡ በዓይኖችህ ፡ ተንቆ
ብላቴናው ፡ ዳዊት ፡ ተቀብቷል ፡ ልቆ
ዓይኔን ፡ ግለጥና ፡ ስፍራዬ ፡ ልወቀው
አሳድገኝ ፡ እንጂ ፡ ዕድሜዬን ፡ አትቁረጠው

አዝ፦ ባስቀመጥከኝ ፡ ቦታ ፡ ፀንቼ ፡ እንድቆይ
መጥተህ ፡ ስትጐበኘኝ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ እንዲልህ
ፀጋህን ፡ አብዛልኝ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እባክህ