አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ (Anten Anten Beyie) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(3)

ክርስቲያን ፡ ተሻገረ
(Christian Teshagere)

ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 2:58
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ
እኔን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ጥዬ
በእምነት ፡ እሻገራለሁ
በድል ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ

ከቀደሙት ፡ ተምሬያለሁ
የአንተን ፡ ተስፋ ፡ እጠብቃለሁ
በምሕረትህ ፡ ተመልከተኝ
እምነትንም ፡ ጨምርልኝ

አዝ፦ አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ
እኔን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ጥዬ
በእምነት ፡ እሻገራለሁ
በድል ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ

የፍየልን ፡ ሌጦ ፡ ለብሰው
መስቀልህን ፡ ተንተርሰው
እየተንከራተቱ ፡ ብዙ ፡ አሉ
ክብራቸውን ፡ ለአንተ ፡ የጣሉ

አዝ፦ አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ
እኔን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ጥዬ
በእምነት ፡ እሻገራለሁ
በድል ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ

በእምነት ፡ ሥምህን ፡ ጠሩ
በፀሎት ፡ ለአንተ ፡ ነገሩ
ከላይ ፡ ሆነህ ፡ ሰማሃቸው
ቃላቸውን ፡ አደመጥካቸው

አዝ፦ አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ
እኔን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ጥዬ
በእምነት ፡ እሻገራለሁ
በድል ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ

በእምነት ፡ ባሕርን ፡ ከፈሉ
ከጠላት ፡ እጅ ፡ አመለጡ
እነርሱን ፡ ልመስል ፡ እሻለሁ
በእምነት ፡ ሥምህን ፡ ጠራለሁ

አዝ፦ አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ
እኔን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ጥዬ
በእምነት ፡ እሻገራለሁ
በድል ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ

በመንፈስ ፡ መልዕክትን ፡ ሰሙ
ጌታ ፡ አንተን ፡ ተሳለሙ
እምነትን ፡ ስጠኝ ፡ እላለሁ
እኔም ፡ አንተን ፡ ለምናለሁ

አዝ፦ አንተን ፡ አንተን ፡ ብዬ
እኔን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ጥዬ
በእምነት ፡ እሻገራለሁ
በድል ፡ ፊትህን ፡ አያለሁ