ተወለደልን (Teweledelen) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በህዝቡ ፡ ሁሉ ፡ የሚሆን
የምሥራች ፡ ተነገረ
ታላቅ ፡ ደስታ ፡ ነው ፡ ልደቱ
ይዘምር ፡ እስኪ ፡ ፍጥረቱ

አዝ፦ መጣ ፡ በራልን ፡ (በራልን)
ጌታ ፡ ሊጐበኘን ፡ (ሊጐበኘን)
ቤዛ ፡ ሊሆንልን
ከኃጢያት ፡ እኛኑ ፡ ሊያድን
ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነና ፡ ከድንግል ፡ ተወለደልን

ህጻን ፡ ተወለደ ፡ ለእኛ
በቤተልሔም ፡ በረት ፡ ተኛ
ለኃጥያተኞች ፡ መዳኛ
ሊሆን ፡ የበጐች ፡ እረኛ

አዝ፦ መጣ ፡ በራልን ፡ (በራልን)
ጌታ ፡ ሊጐበኘን ፡ (ሊጐበኘን)
ቤዛ ፡ ሊሆንልን
ከኃጢያት ፡ እኛኑ ፡ ሊያድን
ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነና ፡ ከድንግል ፡ ተወለደልን

ሥሙ ፡ የተመሰገነ
ክርስቶስ ፡ ጌታ ፡ የሆነ
ተገልጧልና ፡ ልዑሉ
ስገዱለት ፡ ዕልል ፡ በሉ

አዝ፦ መጣ ፡ በራልን ፡ (በራልን)
ጌታ ፡ ሊጐበኘን ፡ (ሊጐበኘን)
ቤዛ ፡ ሊሆንልን
ከኃጢያት ፡ እኛኑ ፡ ሊያድን
ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነና ፡ ከድንግል ፡ ተወለደልን

ተሽቀዳደሙ ፡ ኑ ፡ እዩት
የሚመስልህ ፡ የለም ፡ በሉት
አድንቁት ፡ እጅግ ፡ አክብሩት
ይገባዋል ፡ አመስግኑት

አዝ፦ መጣ ፡ በራልን ፡ (በራልን)
ጌታ ፡ ሊጐበኘን ፡ (ሊጐበኘን)
ቤዛ ፡ ሊሆንልን
ከኃጢያት ፡ እኛኑ ፡ ሊያድን
ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነና ፡ ከድንግል ፡ ተወለደልን

በላይ ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ክብር
ለእኛም ፡ ሰላም ፡ በምድር
ይሁን ፡ ብለን ፡ እንዘምር
እረፍት ፡ አለ ፡ መስቀሉ ፡ ስር

አዝ፦ መጣ ፡ በራልን ፡ (በራልን)
ጌታ ፡ ሊጐበኘን ፡ (ሊጐበኘን)
ቤዛ ፡ ሊሆንልን
ከኃጢያት ፡ እኛኑ ፡ ሊያድን
ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነና ፡ ከድንግል ፡ ተወለደልን