ሁሉን ፡ የምትገዛ (Hulun Yemetgeza) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የጽድቅ ፡ ሥራህን ፡ ጌታ ፡ ሰራህና
በጨለማ ፡ ላሉ ፡ ፀሐይ ፡ ወጣችና
ከዘለዓለም ፡ ጥፋት ፡ አንተ ፡ ያዳንካቸው
በታዳጊነትህ ፡ እጅግ ፡ ደስ ፡ አላቸው (፪x)

አዝ፦ ሁሉን ፡ የምትገዛ ፡ ያለህ ፡ የነበርህ
ትልቁን ፡ ኃይልህን ፡ ለብሰህ ፡ የከበርህ
ሥምህ ፡ ለዘለዓለም ፡ ይመስገን ፡ ይባረክ
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ይንበርከክ

የመስቀል ፡ ፍቅርህን ፡ ለሰው ፡ ይነግራሉ
የቅድስናህን ፡ ክብር ፡ ያወራሉ
በክንፎችህ ፡ ጥላ ፡ ታምነው ፡ ይኖራሉ
የማዳን ፡ ክንድህን ፡ ሁልጊዜ ፡ ያያሉ (፪x)

አዝ፦ ሁሉን ፡ የምትገዛ ፡ ያለህ ፡ የነበርህ
ትልቁን ፡ ኃይልህን ፡ ለብሰህ ፡ የከበርህ
ሥምህ ፡ ለዘለዓለም ፡ ይመስገን ፡ ይባረክ
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ይንበርከክ

ከሥም ፡ ሁሉ ፡ በላይ ፡ ሥምህ ፡ የከበረ
ከሰው ፡ ልጆች ፡ ይልቅ ፡ ውበትህ ፡ ያማረ
የሚመስልህ ፡ የለም ፡ እጅግ ፡ ልዩ ፡ ነህ
ከፍ ፡ ብለህ ፡ ንገሥ ፡ ግርማ ፡ ተሞልተህ (፪x)

አዝ፦ ሁሉን ፡ የምትገዛ ፡ ያለህ ፡ የነበርህ
ትልቁን ፡ ኃይልህን ፡ ለብሰህ ፡ የከበርህ
ሥምህ ፡ ለዘለዓለም ፡ ይመስገን ፡ ይባረክ
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ይንበርከክ

ክብርህ ፡ በምድር ፡ ሁሉ ፡ ይታይ ፡ አምላካችን
ምላስም ፡ ይመስክር ፡ ታላቅነትህን
በሰማይ ፡ በምድር ፡ ትሰለጥናለህ
ሁሉም ፡ ከእግርህ ፡ በታች ፡ አንተ ፡ ትገዛለህ (፪x)

አዝ፦ ሁሉን ፡ የምትገዛ ፡ ያለህ ፡ የነበርህ
ትልቁን ፡ ኃይልህን ፡ ለብሰህ ፡ የከበርህ
ሥምህ ፡ ለዘለዓለም ፡ ይመስገን ፡ ይባረክ
ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ለአንተ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ይንበርከክ (፫x)